Tuesday, September 26, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ ከተቃዋሚ ፓርቲው ትይዩ ሚኒስትር ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ እየተወያዩ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር የክልል ልዩ ኃይሎችን በተመለከተ መንግሥት ያሳለፈው ውሳኔ ላይ ፓርቲያችን ማጣራትና ማረጋገጥ የሚፈልጋቸው ጉዳዮች በመኖራቸው ነው እርስዎን ለማግኘት የጠየቅሁት።
  • ሌሎች ፓርቲዎችም የእናንተን መንገድ ቢከተሉ ጥሩ ነበር።
  • እንዴት?
  • ምክንያቱም አበክረው ሲጠይቁት ለነበረው ጥያቄ መንግሥት ምላሽ ሲሰጥ ጾመኞች ነን አሉ።
  • ክቡር ሚኒስትር እኛም ለመለየት ተቸግረናል።
  • ምኑን?
  • የትኛው የፍስክ፣ የትኛው ደግሞ የጾም እንደሆነ።
  • ለምን?
  • ምክንያቱም አንዳንድ አመራሮች መንግሥት ልዩ ኃይልን የማፍረስም ሆነ የመበተን ፍላጎት የለውም ይላሉ።
  • እውነት ነው።
  • ሌሎች አመራሮች ደግሞ በመንግሥት ውሳኔ መሠረት የክልል ልዩ ኃይሎች ወደ መከላከያ እንደሚቀላቀሉ ይገልጻሉ።
  • ልክ ነው!
  • የቱ ነው ልክ?
  • ሁለቱም፡፡
  • የክልል ልዩ ኃይል አይፈርስም?
  • እኛ ልዩ ኃይልን የማፍረስ ዕቅድ ጨርሶ የለንም። መልሶ የማደራጀት ውሳኔ ነው ያሳለፍነው፡፡
  • ስለዚህ ወደ መከላከያ ይቀላቀላል የሚባለው ትክልል አይደለም?
  • ትክልል ነው እንጂ! ይቀላቀላሉ።
  • ካልፈረሱ እንዴት ሆነው ወደ መከላከያ የሚቀላቀሉት?
  • ምን ችግር አለው? ቀላል እኮ ነው።
  • በምን ዓይነት አደረጃጀት ሊቀላቀሉ ይችላሉ?
  • ማለት?
  • ከተቀላቀሉ በኋላ በመከላከያ ሠራዊት የአማራ ልዩ ኃይል ወይም የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ነው አደረጃጀታቸው?
  • እርስዎም እንደ ሌሎቹ ተቃዋሚዎች ከሥጋው እጾማለሁ ሊሉ ነው?
  • አይደለም፣ ተሳስተዋል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እርስዎ ነዎት የተሳሳቱት፡፡
  • እንዴት?
  • ምክንያቱም የጠቀሱት አደረጃጀት በሙከራ ጭምር የሚያስጠይቅ ነው።
  • የምን ሙከራ?
  • ሕገ መንግሥቱን በኃይል የመናድ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እንዴት እንደዚህ ይላሉ?
  • በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ የሌለ የክልል ልዩ ኃይል አደረጃጀትን ማንሳት ሕግ መንግሥቱን የመናድ ዕሳቤ ቅጥያ ነው!
  • ክቡር ሚኒስትር ከእርስዎ ማብራሪያ ተነስቼ ያልኩት ነው?
  • እኔ እንደዚያ ወጣኝ?
  • መንግሥት የክልል ልዩ ኃይልን የማፍረስ ዕቅድ የለውም ነገር ግን ወደ መከላከያና ሌሎች የፌዴራል የፀጥታ ተቋማት ይቀላቀላሉ አላሉም?
  • ብያለሁ፡፡
  • ታዲያ?
  • እስኪቀላቀሉ ድረስ ነዋ!
  • እንደዚያ ከሆነ ያድርጉልኝ?
  • ከምኑ?
  • ከሥጋውም ከመረቁ!

[የጊዜያዊ አስተዳደሩ መሪ ወደ ሚኒስትሩ ደውለው መንግሥት ሰሞኑን ባወጣው መግለጫ ላይ ማብራሪያ እየጠየቁ ነው]

  • ክብርት ሚኒስትር፣ ሰላም?
  • ሰላም ነኝ፣ ምን እግር ጣለዎት?
  • ምን ስልስ ጣለዎት ነው የሚባለው።
  • ኪኪኪኪ … እውነት ነው። እንዲህ ስንደዋወል ደስ ይላል። ምን ጉዳይ ገጠመዎት?
  • መቼም አንዳንዴ ግርታ አይጠፉም ወይም ያንን ስልት እኛ ላይም መጠቀም ጀምራችሁ ይሆናል።
  • የቱን ስልት?
  • ኮንፊውዝና ኮንቪንስን፡፡
  • እንዴት?
  • መንግሥት ሰሞኑን የሰጠው መግለጫ ግራ አጋብቶናል።
  • ለምን?
  • ክቡር ሚኒስትር በግልፅ እንደሚረዱት የመከላከያ ሠራዊት አካል ያልሆኑ የፀጥታ ኃይሎች ከትግራይ ክልል እንደሚወጡ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ማስፈጸሚያ ተስማምተናል።
  • አዎ። ትክክል ነው።
  • በፕሪቶሪያው ስምምነት ላይ የሰላም ስምምነቱ ዓላማ ተብለው የተዘረዘሩት ነጥቦች አንዱም በቀጥታ ከዚህ ጋር እንደሚገናኝ የሚገነዘቡ ይመስለኛል።
  • ልክ ነው። እስኪ ያስታውሱኝ፣ የትኛው ነጥብ ነበር?
  • በጦርነቱ ምክንያት በትግራይ ክልል የተስተጓጎለውን ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ወደነበረበት መመለስ አንደኛው የስምምነቱ ዓላማ ነው።
  • አዎ። አስታወስኩት። ትክክል ነው።
  • መንግሥት ሰሞኑን የሰጠው መግለጫ ግን ይህንን ያላገናዘበ ይመስላል። በእኛ ላይም ግራ መጋባትን ፈጥሯል።
  • የትኛው መግለጫ ነው?
  • የክልል ልዩ ኃይሎችን በተመለከተ የተሰጠው።
  • ይህ መግለጫ ደግሞ እናንተ ላይ እንዴት ግርታ ይፈጥራል?
  • ፈጥሯል!
  • እኮ እንዴት?
  • ምክንያቱም የክልል ልዩ ኃይሎችን በተመለከተ መንግሥት ያሳለፈው ውሳኔ ከፕሪቶሪያው ስምምነት ጋር አይገናኝም ይላል።
  • ልክ ነው ይላል።
  • እርስዎም ጉዳይ ላይ በሰጡት መግለጫ የመንግሥት ውሳኔ ከሰላም ስምምነቱ ጋር አይገናኝም ብለው ቃል በቃል ደግመውታል።
  • አይገናኝም ብቻ አይደለም ያልኩት፡፡
  • እ…?
  • ከሰላም ስምምነቱም አይጣረስም ብያለሁ!
  • እንደዚያ ማለትዎን አልሰማሁም።
  • እንደዚያ ነው ያልኩት።
  • ከሆነማ መግለጫውም እንደ እርስዎ ነው።
  • እንደ እርስዎ ማለት?
  • ሰላማዊ ነው።
  • ነገር ግን ስምምነቱን ለማስፈጸም ብለን የወሰነው አይደለም።
  • ለምንድነው?
  • የአገራዊ ዕቅዳችን አካል ስለሆነ ነው።
  • ቢሆንም …ክቡር ሚኒስትር ቢሆንም?
  • ቢሆንም ምን?
  • ሚዛናዊ ነው!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

በቀይ ባህር ፖለቲካ ላይ በመከረው የመጀመሪያ ጉባዔ ለዲፕሎማቲክና ለትብብር አማራጮች ትኩረት እንዲሰጥ ጥሪ ቀረበ

ሰሞኑን በአዲስ አበባ ለመጀመርያ ጊዜ በቀይ ባህር ቀጣና የፀጥታ...

የቤት ባለንብረቶች የሚከፍሉትን ዓመታዊ የንብረት ታክስ የሚተምን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በአዋጁ መሥፈርት መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የንብረት ታክስ መጠን...

እንደ ንብረት ታክስ ያሉ ወጪን የሚያስከትሉ አዋጆች ከማኅበረሰብ ጋር ምክክርን ይሻሉ!

የመንግሥትን ገቢ በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የሚታመኑት የተጨማሪ እሴት...

ለዓለምም ለኢትዮጵያም ሰላም እንታገል

በበቀለ ሹሜ ያለፉት ሁለት የዓለም ጦርነቶች በአያሌው የኃያል ነን ባይ...

የመጀመርያ ምዕራፉ የተጠናቀቀው አዲስ አበባ ስታዲየም የሳር ተከላው እንደገና ሊከናወን መሆኑ ተሰማ

እስካሁን የሳር ተከላውን ጨምሮ 43 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጓል ዕድሳቱ...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ለሁለት ቀናት የተካሄደውን የፓርቲያቸውን የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ አጠናቀው ወደ ቢሯቸው ሲመለሱ ቢሯቸው ውስጥ አማካሪያቸው አንድ ጽሑፍ በተመስጦ እያነበበ አገኙት]

ምንድነው እንደዚህ መስጦ የያዘህ ጉዳይ? መጡ እንዴ ክቡር ሚኒስትር፣ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ያወጣውን መግለጫ እያነበብኩ ነው፡፡ ግን እኮ ፊትህ ላይ የመገረም ስሜት ይነበባል፡፡ አዎ፣ መግለጫው ላይ...

[ክቡር ሚኒስትሩ እየጠራ ያለውን ሞባይል ስልካቸውን ተመለከቱ፣ የህዳሴ ግድቡ ተደራዳሪ መሆናቸውን ሲያውቁ ስልኩን አነሱት]

ሃሎ... ጤና ይስልጥኝ ክቡር ሚኒስትር? ጤና ይስልጥልኝ ክቡር ተደራዳሪ... የጥረትዎን ፍሬ በማየትዎ እንኳን ደስ አለዎት፡፡ እንኳን አብሮ ደስ አለን፣ ምን ልታዘዝ ታዲያ? የውኃ ሙሌቱንና አጠቃላይ የግድቡን የግንባታ ሁኔታ...

[የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሩ ክቡር ሚኒስትር ሌሊቱን በእንቅልፍ ልባቸው በህልም እየተወራጩ ሳለ የሞባይል ስልካቸው ጥሪ አነቃቸው። አለቃቸው ስለነበሩ ስልኩን በፍጥነት አነሱት]

በሌሊት ስለደወልኩኝ ይቅርታ፡፡ ችግር የለውም ክቡር ሚኒስትር፣ ምን ልታዘዝ? አንድ የአውሮፓ ባለሥልጣን ነገ በጠዋት ወደ አዲስ አበባ ይገባል። እሺ። ሌሎች የመንግሥት አመራሮች ስላልቻሉ እርስዎ መንግሥትን ወክለው ቦሌ ኤርፖርት...