Tuesday, September 26, 2023
Homeስፖንሰር የተደረጉበኢትዮጵያ የአየርላንድ ኤምባሲ - የጉድ ፍራይዴይ ስምምነት 25 ዓመታት: ስለ ሰላም ስናስብ

በኢትዮጵያ የአየርላንድ ኤምባሲ – የጉድ ፍራይዴይ ስምምነት 25 ዓመታት: ስለ ሰላም ስናስብ

Published on

- Advertisment -

የአየርላንድ፣ የሰሜን አየርላንድ እና የብሪታንያ ህዝቦች ሚያዚያ 2 ቀን 2015 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ. ኤፕሪል 10 ቀን 2023 ዓ.ም.) በአየርላንድ ደሴት ውስጥ የተለያዩ ፖለቲካዊ ልማዶች ያሏቸው መሪዎች ከያሉበት በመሰባሰብ የጉድ ፍራይዴይ ስምምነትን የፈረሙበትን 25ኛ አመት የአየርላንድ ደሴት የፖለቲካ ያከብራሉ። ልክ እንደ ኢትዮጵያው ጠላትነትን በዘላቂነት የማቆም ስምምነት ሁሉ፣ የጉድ ፍራይዴይ የሰላም ስምምነትም እንደ አንድ ታላቅ ኩነት ውዳሴን ተችሯል። ይኽ የጉድ ፍራይዴይ ስምምነት ለአየርላንድ እና ዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) የሰላም፣ የጸጥታ እና የመረጋጋት ዘመንን አምጥቷል፣ ማህበረሰቦችን ከፋፍሎ የብዙዎችን ህይወት ያለጊዜያቸው ያጠፋውን የ 30 አመታት አሰቃቂ የግጭት ምዕራፍን ዘግቷል። ስምምነቱ የአመጽና የሁከት ፖለቲካን ውድቅ ለማድረግ እና የማንነት ብዝሃነትን እና የአየርላንድን የሰሜን እና ደቡብ ህዝቦችን ፍላጎት ያቀፈ ግንኙነት አዲስ ማዕቀፍ ለመፍጠር የተደረገ ውሳኔ ነበር።

ስምምነቱ በአየርላንድ እና በእንግሊዝ የጋራ ታሪክ ውስጥ ልዩና ወሳኝ ከመሆኑም ባሻገር ለህዝባችን የተሻለ የወደፊት ሁኔታን ለማረጋገጥ በደሴቶቻችን ውስጥ እና መካከል ያለውን ግንኙነት ለመለወጥ የጋራ ቁርጠኝነትን ያሳያል። አሁን ከ 25 አመታት በኋላም፣ ይኽንን ድንቅ ድል ማክበራችን እና አየርላንድ የ 1990 አመተ ምህረቱን የርዕይ መንፈስንና አመራሯን ዛሬ ላይ እያጋጠሙ ላሉት አለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች እንዴት አድርጋ እንደምታጋራ ማሰቧ በእርግጥም ትክክለኛ ነገር ነው።

ባለፉት 25 ዓመታት፣ ሰላም እና እርቅ ሊመጣ የሚችለው ግጭት ውስጥ ያሉ ወገኖች ልዩነታቸውን ወደ ጎን በመተው ለሁሉም መሻሻል ሲሰሩ ብቻ እንደሆነ አየርላንድ ተገንዝባለች። የሰሜን አየርላንዱ የሰላም አቀንቃኝ ጆን ሂዩም የጉድ ፍራይዴይ የሰላም ስምምነትን እውን ለማድረግ ባደረጉት ጉልህ አበርክቶ የሰላም የኖቤል ሽልማታቸውን ሲቀበሉ በአጽናኦት እንደተናገሩትም፣ “ልዩነት የሰብአዊ ፍጡር መለያ ማንነቱ ነው። ለልዩነት የሚሰጠው ምላሽ ልዩነትን ማክበር ነው። እዚህ ውስጥም መሰረታዊው የሰላም መርሆ ይገኛል – ብዘሃነትን ማክበር።”

እነዚህ መርሆዎች ሰላምን በመገንባት ሂደት ውስጥ ሁሉም ድምፆች መደመጣቸውን እና መከበራቸውን ማረጋገጥ አለባቸው። በሰሜን አየርላንድ ውስጥ በተለይ የሴቶች ድምጾች ያለመደመጥ አደጋ ውስጥ መደቃቸውን ተረድተናል። የሰሜን አየርላንድ ሴቶች ዜጎች በሰላሙ ሂደት ውስጥ የሚገባቸውን ቦታቸውን ለማግኘት መታገል ነበረባቸው፤ ተገቢ ቦታቸውን ባገኙ ጊዜም ሰላምን ለማስፈን እና ለማስቀጠል ግዙፍ አስተዋፅዖን ለማበርከት ችለዋል። የሴቶች ድምፅ ችላ አለመባሉን ማረጋገጥ በጣም አስፈላጊ ነው – ሴቶችን ፣ ወጣቶችን እና ብዝሃ የፖለቲካ አስተያየቶችን ያላካተተ ሂደት ለዘላቂ ሰላም ጠንካራ መሠረት ሊሆን አይችልም።

በሰሜን አየርላንድ ውስጥ የሰላም ሂደቶች የሳምንታትን፣ የወራትን፣ የዓመታትን ግዙፍ፣ ቀጣይነት ያለው ጥረት፣ ጽናት፣ ትዕግስት እና እምነት እንደሚፈልጉም ተገንዝበናል። በወሳኝ መልኩ፣ ይህ ቁርጠኝነት አዎንታዊ ምላሹን ያገኘው ሚያዚያ 2 ቀን 1990 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ. ኤፕሪል 10 ቀን 1998 ዓ.ም.) አዲስ እውነት ሲመሰረት ነበር። ይኽ የጉድ ፍራይዴይ የሰላም ስምምነት – የማይመስል፣ የማይቻል ይመስል የነበረው ስምምነት – በእርግጥም የሚቻል መሆኑን አሳይቷል። ይኽ ሁል ጊዜም የተስፋ እና የመጽናኛ ምንጭ እና በሰላም ላይ ያለው እምነትም ከማንኛውም አማራጭ የተሻለ ለመሆኑ እንደ አንድ መነሳሻ ሆኖ መዝለቅ አለበት።

ሆኖም ግን፣ ከ 25 አመታትም በኋላ፣ ታሪካዊ ክስተቶችን ማወደሱ ብቻ አደጋ ሊኖረው ይችላል። የጉድ ፍራይዴይ የሰላም ስምምነት ፍጹም አለመሆኑን ማስታወስ አስፈላጊ ነው። የትኛውም የሰላም ስምምነት ፍጹም አይደለም። የአየርላንድ ምክትል ጠቅላይ ሚ/ር የሆኑት ማይክል ማርቲን በቅርቡ እንደተናገሩት፣ “የትኛውም የአየርላንድ ማህበረሰብ በ 1990ው ስምምነት የተመኛቸውን ሁሉ አላገኘም፣ እያንዳንዱ ሰው ግን ሰላምን አግኝቷል። የጉድ ፍራይዴይ የሰላም ስምምነት መፈረም ጅማሮም ፍጻሜም ነበር። የስምምነቱ መፈረም ሁሉም ወገኖች ለአመታት ያከናወኗቸው ጠንካራ ስራዎች እና አስቸጋሪ ሰጥቶ መቀበሎች ፍጻሜ ያገኙበት ነበር። የስምምነቱ መፈረም የሰላም ግንባታ፣ የእርቅ እና ለተለየ ግን ደግሞ እጅግ ለተሻለ መጻኢ ጊዜ አዲስ ሂደት ጅማሮም ነበር።”

ኢትዮጵያም አስደናቂ ድል የሆነውን የራሷን ጠላትነቶችን በዘላቂነት የማቆም ስምምነት በምታስብበትም ወቅት፣ አየርላንድ በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ሁከትና ብጥብጥ ማብቃቱን እና የተሻለች ኢትዮጵያን ለሁሉም ተጠቃሚ እንድትሆን በሁሉም ወገን ያለውን ቁርጠኝነት በደስታ ትቀበላለች። ከግጭት በኋላ በማንኛውም የድህረ-ግጭት አውድ ውስጥ ስሜታዊ፣ ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና አካላዊ ጠባሳዎቹ ስር ይሰዳሉ። አስቸጋሪው እርቅን እውን የማድረግ ስራ በርካታ አመታትን እና ከፍተኛ ጥረትን ይጠይቃል። የሚነሱትን ችግሮች ሁሉ ተቋቁሞ ሰላም እንዲጠበቅ ማድረግ የእኛ ኢትዮጵያ ውስጥ የምንኖር ሰዎች ግዴታና ኃላፊነት ነው። አየርላንድ የሰላም ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዲሆን ለመደገፍ እና ለመላው ኢትዮጵያውያንም ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ የበኩሏን አስተዋጽኦ ለማድረግ ዝግጁ ነች።

የቅርብ ጊዜ መጣጥፎች

በቀይ ባህር ፖለቲካ ላይ በመከረው የመጀመሪያ ጉባዔ ለዲፕሎማቲክና ለትብብር አማራጮች ትኩረት እንዲሰጥ ጥሪ ቀረበ

ሰሞኑን በአዲስ አበባ ለመጀመርያ ጊዜ በቀይ ባህር ቀጣና የፀጥታ እንቅስቃሴ ላይ በመከረው ጉባዔ፣ ኢትዮጵያ...

የቤት ባለንብረቶች የሚከፍሉትን ዓመታዊ የንብረት ታክስ የሚተምን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በአዋጁ መሥፈርት መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የንብረት ታክስ መጠን ይወስናሉ በ1968 ዓ.ም. የወጣውን የቦታ ኪራይና...

እንደ ንብረት ታክስ ያሉ ወጪን የሚያስከትሉ አዋጆች ከማኅበረሰብ ጋር ምክክርን ይሻሉ!

የመንግሥትን ገቢ በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የሚታመኑት የተጨማሪ እሴት ታክስ መሻሻያ አዋጅና የንብረት አዋጅ...

ለዓለምም ለኢትዮጵያም ሰላም እንታገል

በበቀለ ሹሜ ያለፉት ሁለት የዓለም ጦርነቶች በአያሌው የኃያል ነን ባይ አገሮች ጎራዊ ግጥሚያዎች ነበሩ፡፡ በእነዚህ...

ተመሳሳይ

በአፍሪካ የገንዲ በሽታ ስርጭትን ለመግታት የሚያስችሉ መፍትሄዎች ላይ በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ ተደረሰ

የአፍሪካ እንስሳት ትራይፓኖሶሚያሲስ (AAT) በመባል የሚታወቀው የገንዲ በሽታ ከሰሃራ በታች ባሉ አፍሪካውያን የእንስሳ እርባታ...

ታምሪን ሞተርስ አዲስ ያስመጣዉን ሱዙኪ ኢኮ ቫን ሞዴል በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ

ለአካባቢ ሥነ ምህዳር ምቹ የሆኑ ተሽከርካሪዎችን ከሚያመርተው እና በዓለም ታዋቂ ከሆነው የሱዙኪ ኩባንያ ጋር...

የላይፍላይን አዲስ የቤት ለቤት ጤና እንክብካቤ አገልግሎት ድርግጅት በጤናው ዘርፍ የቁርጥ ሥራ (ጊግ) ኢኮኖሚን የመገንባት ጉዞ

ዶ/ር ሰለሞን ደሳለኝ  ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ በሕክምና የተመረቀው በ2009 ዓ.ም. ማብቂያ...