Thursday, June 1, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው?
  • ምነው?
  • ምክር ቤቱም ሆነ አባላቱ የተከበሩ ተብለው የሚጠሩት በምክንያት አይደለም እንዴ?
  • ትክክል ነው። ምክንያቱም፣ ምክር ቤቱ ትልቁ የሥልጣን አካል ነው፣ አባላቱም የሕዝብ ተወካዮች በመሆናቸው የተከበሩ ተብለው ነው የሚጠሩት።
  • ታዲያ ዝም ማለት ተገቢ ነው፣ መገሰጽ የለብንም?
  • ምኑን?
  • የተከበረው ምክር ቤት አባል ያቀረበውን ጥያቄ ‹‹ጥሩ ቀልድ ነው›› ሲሉ ዝም ማለት ተገቢ ነው?
  • እርስዎም እኮ በማይመጣው ነው የመጡት።
  • እንዴት?
  • ሥልጣን ይልቀቁ ነዋ ያሉት?
  • እንደዚያ ከሆነ ምክር ቤቱ አንድ ቋሚ ኮሚቴ ሊያቋቁምልን ይገባል።
  • የምን ቋሚ ኮሚቴ?
  • የቀልድ ጉዳዮች!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከተቋሙ ሠራተኞች ማኅበር ጋር ስለ የመደመር ትውልድ መጽሐፍ ሽያጭ እየተወያዩ ነው]

  • ጤና ይስጥልኝ ክቡር ሚኒስትር?
  • ሰላም፡፡
  • በአስቸኳይ እንደፈለጉኝ መልዕክት ደርሶኝ ነው የመጣሁት።
  • አዎ። ይህንን ደብዳቤ እየውና በጠየቁት መሠረት ይፈጸምላቸው።
  • ጉዳዩ ምንድነው?
  • ከኦሮሚያ ክልል የመጣ ደብዳቤ ነው። የተቋማችንን ትብብር ይፈልጋሉ።
  • የምን ትብብር ነው የጠየቁት?
  • የመደመር ትውልድ መጽሐፍን በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱና በተጠሪ ተቋማት ለሚገኙ ሠራተኞች በመሸጥ ገቢውን እንድናስገባላቸው ነው የጠየቁት።
  • ምን…?
  • የመደመር ትውልድ መጽሐፍን ለተቋማችን ሠራተኞች እንድንሸጥላቸው ነው የጠየቁት። ከደብዳቤው ጋር አያይዘውም ሁለት ሺሕ መጽሐፍቶችን ልከውልናል።
  • ክቡር ሚኒስትር ማለት የምችለው አንድ ነገር ብቻ ነው።
  • ምን?
  • አድርሰናል!
  • እንዴት? ምን ማለትህ ነው?
  • ተመሳሳይ የትብብር ጥያቄ ሰሞኑን ቀርቦልን አስተናግደናል።
  • ማነው የጠየቀው?
  • የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር።
  • ይህንኑ መጽሐፍ እንድንሸጥ ነው የጠየቁት?
  • አዎ። እነሱም ሁለት ሺሕ መጽሐፍ ነበር የላኩት።
  • እና ምን ምላሽ ሰጣችኋቸው?
  • በዋናው መሥሪያ ቤትና በተጠሪ ተቋማት ያሉ ሠራተኞችን አስቸግረን ከሞላ ጎደል ያቀረቡት መጽሐፍ ተሽጦላቸዋል።
  • በፌዴራል ተቋማት እንዲሸጡ ማን ፈቀደላቸው?
  • እንዴት?
  • መሸጥ የነበረባቸው በተከማ አስተዳደሩ ተቋማት ሥር ለሚገኙ ሠራተኞች እንጂ በፌዴራል ተቋማት ውስጥ ሽጡ አልተባሉማ፡፡
  • ኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥትም ወደ እኛ ተቋም መላክ አልነበረበትም።
  • እንዴት?
  • መጽሐፉን በራሱ ክልል ውስጥ ሸጦ ገቢውን ለተባለው ፕሮጀክት እንዲያውል ነዋ የታዘዘው።
  • አዲስ አበባ የክልሉ መንግሥት መቀመጫ መሆኗን እያስተዋልን እንጂ?
  • መቀመጫ መሆኗንማ አውቃለሁ።
  • ታዲያ ምንድነው የምትለው?
  • መቀመጫ ብቻ ነዋ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • የመጽሐፍ ሽያጭን አስታከህ የሕገ መንግሥት ጥያቄ እያነሳህ ነው?
  • የሕገ መንግሥት ጥያቄ?
  • አዎ። ዳርዳር እያልክ ያለኸው ምን ልታነሳ እንደሆነ ያስታውቃል።
  • ኧረ እኔ ዳርዳር አላልኩም፣ የማነሳው ጥያቄም የለኝም።
  • አዲስ አበባ መቀመጫ ብቻ ነች አላልክም።
  • እሱንማ ብያለሁ።
  • ታዲያ ይኼ ምን ማለት ነው?
  • ምን ማለት ነው?
  • አዲስ አበባ የኦሮሚያ አይደለችም እያልክ ነዋ!
  • ክቡር ሚኒስትር እኔ እንደዚያ አልወጣኝም፣ አላልኩም!
  • መቀመጫ ብቻ ነች ማለት ምን ማለት ነው ታዲያ?
  • ክቡር ሚኒስትር የተፈለገው የመደመር ትውልድ መጽሐፍን መሸጥ አይደል?
  • የጠየቁት እሱን ነው!
  • ስለዚህ በሐሳብ መለያየት ያለብን አይመስለኝም። በዚያ ላይ…
  • እ… በዚያ ላይ ምን?
  • የመጽሐፉ ይዘትም ተደመሩ ነው የሚለው።
  • ስለዚህ?
  • መከራከራችን ትክክል አይደለም፣ ይጋጫል።
  • ከምንድነው የሚጋጨው?
  • ከመጽሐፉ መንፈስ ጋር ይጋጫል። አብሮ አይሄድም።
  • ስለዚህ መጽሐፉ እንዲሸጥ ታደርጋለህ።
  • ያው ሠራተኛው አንድን መጽሐፍ ለሁለተኛ ጊዜ ግዛ ብንለው የሚሰጠው ምላሽ ይታወቃል።
  • ምን ሊል ይችላል?
  • አንብቤ ስጨርስ ፓስታ ይሆናል እንዴ ብሎ ማሾፉ አይቀርም።
  • ስለዚህ?
  • እኔ ሌላ መፍትሔ እፈልጋለሁ።
  • ምን ዓይነት መፍትሔ?
  • ከድርጅቱ ወጪ ሆኖ መጽሐፉን በሠራተኞች ስም እንገዛለን።
  • መጽሐፍ ለመግዛት የተፈቀደልን በጀት የለማ፣ ኦዲት ስንደረግ ምን ልትል ነው?
  • ወጪውን ለመጽሐፍ ግዢ የዋለ አንለውም።
  • እና ምን ልትለው ነው?
  • ለመደመር ብለን እንመዘግበዋለን።
  • ኦዲተሩ ቢጠይቅስ?
  • ወጪው በመደመር ስም ተይዞ?
  • እ…?
  • አይጠይቅም!
  • እንደዚያ ከሆነማ ሃያ ሺሕ አድርገው።
  • ምኑን?
  • የመጽሐፉን ብዛት!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

በኦሮሚያ ክልል በስድስት ከተሞች የተዋቀረውን ሸገር ከተማን የማደራጀት ሥራ ተጀመረ

በአዲስ አበባ ዙሪያ በሚገኙ ስድስት ከተሞች የተዋቀረው ሸገር ከተማን...

ኢንቨስተሮች አደጋ ሲገጥማቸው ድጋፍ ማድረግ የሚያስችለው መመርያ ተሻረ

በተፈጥሮና በሰው ሠራሽ አደጋዎች በኢንቨስተሮች ንብረት ላይ አደጋ ቢከሰት፣...

የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ አልባ በማድረግ ታሪክ አይሠራም

በኢተፋ ቀጀላ​​  ከዛሬ ሃምሳ ዓመት ወዲህ ከተፈጠሩት የኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ከኢጭአት በስተቀር፣...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...

የባንኮች ብድር አሰጣጥ ፍትሐዊና ብዙኃኑን ያማከለ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

ባንኮች የብድር አገልግሎታቸውን በተቻለ መጠን ፍትሐዊ፣ የብዙኃኑን ተጠቃሚነት ያማከለና...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል። ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ...