Tuesday, March 28, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

  • ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት።
  • እሺ ምንን በተመለከተ ነው?
  • የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው።
  • የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን?
  • የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ ተፈቅዶላቸዋል?
  • ቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ የሚፈቅድ ሕግ ያለ አይመስለኝም። ግን ደግሞ በአንድ ነገር እርገጠኛ ነኝ።
  • በምን ክቡር ሚኒስትር?
  • እንዳይሸጡ የሚከለክል ሕግ አለመኖሩን!
  • ስለዚህ መሸጥ ይችላሉ ማለትዎ ነው?
  • አላልኩም፡፡
  • ታዲያ ምን እያሉኝ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • የሚከለክል ሕግ እንደሌለ እርግጠኛ ነኝ ነው ያልኩት።
  • በእኛ ባደረግነው ማጣራት ደግሞ የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ የሚፈቅድ ሕግ የለም። ስለዚህ…
  • እ… ስለዚህ ምን?
  • የሚከለክል ሕግ ከሌለ እንደተፈቀደ ይቆጠራል ማለት እንችላለን ማለት ነው?
  • ከሕግ ትርጓሜ አኳያ ከተመለከትነው እንደዚያ ማለት ነው። ግን ለምንድነው ማጣራት የፈለጋችሁት?
  • በዚህ ሥራ ፈቃድ ያወጡ አስመጪዎች እያሉ አንድ የቴሌኮም ኩባንያ ሰሞኑን ውድ ስልኮችን አስመጥቶ ለገበያ እያስተዋወቀ ስለሆነ ነው።
  • ውድ ስልኮችን ስትል ምን ያህል የሚያወጡ ናቸው?
  • ትንሹ ዋጋ 95,000 ብር ነው።
  • ትልቁ ዋጋስ?
  • ትልቁ ዋጋ 140,000 ነው።
  • የትኛው የቴሌኮም ኩባንያ ነው?
  • የእኛው ነው።
  • ነው? ገባኝ፣ ገባኝ!
  • ምን ገባዎት ክቡር ሚኒስትር?
  • ለማን ሊያቀርብ እንደሆነ፡፡
  • ለማን ሊያቀርብ ነው?
  • ለከተማ አስተዳደሩ።
  • የትኛው ከተማ አስተዳደር?
  • ለአመራሮቹ የ140,000 ብር ስልክ እንዲገዛ የወሰነው አስተዳደር።
  • ለአመራሩ በጥቅማ ጥቅም መልክ እንዲሰጥ ነው የተወሰነው ክቡር ሚኒስትር?
  • አዎ። እንደዚያ ነው የተባለው።
  • የጥቅማ ጥቅም ውሳኔ መባሉ ግን ትክክል አይመስለኝም።
  • ታዲያ ውሳኔው ምን መባል ነበረበት?
  • ጋላክሲ ኤስ 23!
  • ኪኪኪኪ… የአስተዳደሩን ውሳኔ እንደዚያ ካልክ የቴሌኮም ኩባንያውን ውሳኔም ምን ልትለው ነው?
  • የድርሻዬን!

[የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ በስንዴ ምርት ግዥ ላይ ግር ያላቸውን ለማጥራት ለፌዴራሉ አቻቸው ጋ ስልክ ደወሉ]

  • በመኸር ወቅት የተሰበሰበው ስንዴ ለገበያ የሚቀርብበትን መንገድ የተመለከተ መመርያ ከገንዘብ ሚኒስቴር ደርሶን ነበር።
  • እሺ፡፡
  • እርስዎ ደግሞ ሰሞኑን ለሚዲያ የተናገሩትና ማሳሰቢያ አዘል መግለጫ አለ።
  • እሺ፡፡
  • እርስዎ የሰጡት ማሳሰቢያና ከገንዘብ ሚኒስቴር የደረሰን መመርያ የሚጣረሱ በመሆናቸው ነገሩን ለማጥራት ብዬ ነው።
  • ከገንዘብ ሚኒስቴር የደረሳችሁ መመርያ ምን ይላል?
  • የተመረተውን ስንዴ መግዛት የሚችሉት ከመንግሥት ጋር በትብብር የሚሠሩ ማኅበራትና ዩኒየኖች ብቻ ናቸው ይላል።
  • ትክክል ነው።
  • ማኅበራትና ዩኒየኖቹ ስንዴ መግዣ እንዳይቸገሩም ለክልሉ 1.3 ቢሊዮን ብር መላኩን ይገልጻል።
  • አዎ። ለሁሉም ሰንዴ አምራች ክልሎች በጀት መመደቡን አውቃለሁ፡፡
  • የደረሰን መመርያ የስንዴ መሰብሰቢያ ዋጋንም ያካተተ ነው።
  • መሰብሰቢያ ማለት?
  • አርሶ አደሩ የትርፍ ህዳግን ጨምሮ ስንዴ የሚሸጥበት ከፍተኛ ዋጋ ብር 3,200 መሆኑን አሳውቆናል።
  • ትክክል ነው።
  • እኛም በዚህ መሠረት ማንኛውም ዱቄት ፋብሪካና ነጋዴ ስንዴ እንዳይገዛ አግደናል። ምክንያቱም የዩኒየኖቹ የስንዴ ፍጆታ እንዳይጎድል በማሰብም።
  • ትክክል ነው፣ ምክንያቱም የዩኒየኖቹ የስንዴ ፍጆታ መሟላት አለበት።
  • ነገር ግን እርስዎ ሰሞኑን የሰጡት መግለጫ ችግር ፈጥሮብናል።
  • የትኛው መግለጫ?
  • አርሶ አደሩ ከ3,200 ብር በላይ የሚገዛው ካገኘ ስንዴውን መሸጥ ይችላል፣ የከለከለው የለም ብለው የተናገሩት።
  • እሱን የተናገርኩት የዩኒየኖቹ የስንዴ ፍጆታ ለማስተጓጎል አይደለም።
  • ታዲያ ለምንድነው?
  • ለሚዲያ ፍጆታ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ አልባ በማድረግ ታሪክ አይሠራም

በኢተፋ ቀጀላ​​  ከዛሬ ሃምሳ ዓመት ወዲህ ከተፈጠሩት የኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ከኢጭአት በስተቀር፣...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...

ጉራጌን በክላስተር ለመጨፍለቅ የሚደረገውን ጥረት እንደሚቃወም ጎጎት ፓርቲ አስታወቀ

ለጉራጌ ሕዝብ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበር እንደሚታገል የሚናገረው አዲሱ...

‹‹ኢኮኖሚው ላይ የሚታዩ ውጫዊ ጫናዎችን ለመቀልበስ የፖሊሲ ሪፎርሞች ያስፈልጋሉ›› ዓለም ባንክ

በዓለም ደረጃ ከተፈጠረው የኢኮኖሚ አለመረጋጋት ጋር በተገናኘ፣ በኢትዮጵያ ውጫዊ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

‹‹ከኦነግ ሸኔ ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት አለን›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ

መንግሥት ከ‹‹ኦነግ ሸኔ››ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት...

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...

[የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣን በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለመመካከር በሚኒስትሩ ቢሮ ተገኝተው ውይይታቸውን ጀምረዋል]

ክቡር ሚኒስትር ባላንጣዎቻችን የእኛኑ ስልት መጠቀም የጀመሩ ይመስላል። እንዴት? ምን አዲስ ነገር ተፈጠረ? እስከዛሬ እኛ የምንሰጣቸውን አጀንዳ ተቀባይ ነበሩ። በዚህም በውስጣቸው ልዩነትንና አለመግባባትን መትከል ችለን ነበር። አሁን...