Thursday, March 23, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ኪንና ባህልአማልክቶቼ ሆይ በፍሬዴሪክ ኸልደርሊን (1770 - 1843)

አማልክቶቼ ሆይ በፍሬዴሪክ ኸልደርሊን (1770 – 1843)

ቀን:

ታገሱኝ ኃያላን በጋውን፥

እንዲሁም መጸውን፥

እስክጽፈው ግጥሜን፡፡

ያኔ ልቤ እያዜመ በታላቅ ደስታ፥

ፈቃዱ ይሆናል ለዘለዓለማዊ እንቅልፍ ለመኝታ፡፡

ግልጽ ነው አውቃለሁ የአርባ ቀን ዕድሏን ያልተቀበለች ነፍስ፥

ልትመኝ ቀርቶባት ገነትን ለመውረስ፥

ከወዲያኛው ዓለም አትችልም ለመድረስ፡፡

ግን ጊዜን ተችሮኝ ያንን ቅዱስ ተግባር ከቻልኩ ለመፈጸም፥

ከልቤ አመንጭቼ ከገጠምኩኝ ግጥም፥

ከወቀሳም ድኜ አገኛለሁ ሰላም፡፡

ያለማወላወል እቀበለዋለሁ በጸጋ ሞትንም፡፡

እንደ አማልክት ሁሉም ሰማይ እኖራለሁ፡፡

ከዚያ ወዲያ ተድላ ምን እፈልጋለሁ፡፡

  • ተርጓሚዎች እነ ዘሪሁን አስፋው ‹‹የጀርመን ቅኔያት ከወልፍጋንግ ገተ እስከ ጉንተር ግራስ›› (1993 ዓ.ም.)
spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...