Thursday, November 30, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ኪንና ባህልአማልክቶቼ ሆይ በፍሬዴሪክ ኸልደርሊን (1770 - 1843)

አማልክቶቼ ሆይ በፍሬዴሪክ ኸልደርሊን (1770 – 1843)

ቀን:

ታገሱኝ ኃያላን በጋውን፥

እንዲሁም መጸውን፥

እስክጽፈው ግጥሜን፡፡

ያኔ ልቤ እያዜመ በታላቅ ደስታ፥

ፈቃዱ ይሆናል ለዘለዓለማዊ እንቅልፍ ለመኝታ፡፡

ግልጽ ነው አውቃለሁ የአርባ ቀን ዕድሏን ያልተቀበለች ነፍስ፥

ልትመኝ ቀርቶባት ገነትን ለመውረስ፥

ከወዲያኛው ዓለም አትችልም ለመድረስ፡፡

ግን ጊዜን ተችሮኝ ያንን ቅዱስ ተግባር ከቻልኩ ለመፈጸም፥

ከልቤ አመንጭቼ ከገጠምኩኝ ግጥም፥

ከወቀሳም ድኜ አገኛለሁ ሰላም፡፡

ያለማወላወል እቀበለዋለሁ በጸጋ ሞትንም፡፡

እንደ አማልክት ሁሉም ሰማይ እኖራለሁ፡፡

ከዚያ ወዲያ ተድላ ምን እፈልጋለሁ፡፡

  • ተርጓሚዎች እነ ዘሪሁን አስፋው ‹‹የጀርመን ቅኔያት ከወልፍጋንግ ገተ እስከ ጉንተር ግራስ›› (1993 ዓ.ም.)
spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...