Tuesday, March 28, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

  • እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ?
  • በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው።
  • ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው ነው?
  • ክቡር ሚኒስትር እነሱ እንደዚያ አላደርግንም፣ የፌዴራል መንግሥት ሳያጸድቀው የሽግግር መንግሥት አይመሠረትም እያሉ ነው።
  • ታዲያ ምንድነው የሠሩት?
  • ረቂቁን ነው የሠሩት።
  • ረቂቅ ምን?
  • ረቂቅ መንግሥት።

[ክቡር ሚኒስትሩ ከባልደረቦቻቸው ጋር ሆነው የከተማ አስተዳደሩን ኃላፊ እየገመገሙ ነው]

  • ባለፈው በተገናኘንበት ወቅት የተለያዩ ማሳሰቢያዎችን ሰጥቼ ነበር።
  • አዎ። ትክልል ነው ክቡር ሚኒስትር
  • ለምሳሌ በሁሉም የከተማዋ ክፍሎች በ90 ቀን መፈጸም የሚችሉ ፕሮጀክቶች ተለይተው እንዲተገበሩ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቼ ነበር።
  • አዎ።
  • እኮ ከምን ደረሰ?
  • በሁሉም የከተማው ክፍሎች ተጀምሯል። በተለይ በአዲሱ ክፍለ ከተማ አመቺ ቦታ በመኖሩ የተለያዩ የ90 ቀን ፕሮጀክቶችን እየተገበርን እንገኛለን።
  • ለምሳሌ ምን ተተገበረ?
  • የጓሮ አትክልቶችና መመገቢያ ማዕከላትን አጠናቀናል በተጨማሪም የከብት ዕርባታ ፕሮጀክት…
  • ከብት ዕርባታ በ90 ቀን?
  • ከብቶቹ በ90 ቀን እንደማይደርሱ የተረዳነው ፕሮጀክቱን ከጀመርን በኋላ ነው።
  • ስለዚህ ፕሮጀክቱ ታጠፈ?
  • አልታጠፈም። መፍትሔ አበጅተንለታል።
  • ምን አደረጋችሁ?
  • የደረሱ ከብቶችን ለይተን አስገብተናል።
  • ለምን የደረሱ?
  • ለመታለብ።
  • ማሳሰቢያ የሰጠሁት ግን ለአንድ ክፍለ ከተማ ብቻ አይደለም።
  • ልክ ነው ክቡር ሚኒስትር።
  • አመራሩ ቢሮ መዋልና በቪኤይት መንፈላሰስ ከዚህ በኋላ አይችልም። ፒክአፕ እየነዳ ፕሮጀክቶችን ይከታተል ብዬ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቼ እንዴት እስካሁን አይጀመርም?
  • በማሳሰቢያው መሠረት የከተማ አመራሩ ቪኤይት እንዳይነዳ ከልክለን ጎን ለጎን የጀመርነውን ጨረታ ሰሞኑን አጠናቀናል።
  • የምን ጨረታ?
  • የፒክ አፕ።
  • ምን?
  • አመራሩ ፒክ አፕ እየነዳ ፕሮጀክቶችን እንዲከታተል በሰጡት ማሳሰቢያ መሠረት የተፈጸመ ነው።
  • አመራርነት በቪኤይት መንፈላሰስ አይደለም ብል ፒክ አፕ ገዛችሁ?
  • በግልጽ እኮ ነው የገዛነው?
  • በግልጽ ማለት?
  • በግልጽ ጨረታ።
  • እሺ ሌላስ ምን ገዛችሁ?
  • አመራሩ ፒክ አፕ ቢመደብለትም ቢሮ መዋሉን ሊተው ባለመቻሉ ይህንን የሚያስቀር ግዥ እንዲፈጸም ወስነናል።
  • የምን ግዥ?
  • ለእያንዳንዱ አመራር በደረጃው ልክ ዘመናዊ ላፕቶፕና ሞባይል ስልክ እንዲገዛ።
  • ምን?
  • አዎ። ከዚህ በኋላ ቢሮ ለመዋል ምክንያት አይኖራቸውም። ባሉበት ሆነው በስልካቸው ወይም በላፕቶፕ መገልገል ይችላሉ።
  • እኔ ያልኩት ሕዝብ እንድታገለግሉና ቢያንስ የአቅመ ደካሞችን ቤት እንድታድሱ፣ እንድትጠግኑ እንጂ …
  • ክቡር ሚኒስትር ስለእሱም ተወያይተን ወስኔ አሳልፈናል።
  • ምን?
  • አመራሩ የአቅመ ደካሞችን ቤት ለማደስ እንዲነሳሳ ይጠቅማል ያልነውን ወሳኔ አሳልፈናል።
  • ምን ወሰናችሁ?
  • ቤት ለሌለው አመራር ቤት እንዲሰጥ ቤት ላለው ደግሞ…
  • እሺ… ቤት ላለው ምን?
  • ቤቱን የሚያድስበት ወጪ በአስተዳደሩ እንዲሸፈን ወስነናል።
  • ወሰናችሁ?
  • አዎ። ከዚህ በኋላ የአቅመ ደካሞችን ቤት ላለማደስ ማቅማማት አይችሉም፣ ምክንያትም አይኖራቸውም።
  • እኔም ሳላቅማማ አድሰዋለሁ!
  • ምኑን?
  • ካቢኔውን!

[የከተማ አስተዳደሩ ኃላፊ ከስብሰባው ከወጡ በኋላ ወደ ሚኒስትሩ ስልክ ደወሉ]

  • ክቡር ሚኒስትር ቅድም የተናገሩት የምርዎትን እንዳልሆነ ተስፋ አደርጋለሁ?
  • የሕዝብ ሀብት እየባከነ እንዴ እቀልዳለሁ?
  • ክቡር ሚኒስትር ሀብት እያባከንን አይደለም።
  • ታዲያ ሌላ ምን ሊባል ነው?
  • ቅድም ብቻዎትን ስላልነበሩ ተቆጥቤ እንጂ ምክንያቱ ሌላ ነው።
  • ሌላው ምክንያት ምንድነው?
  • ክቡር ሚኒስትር እኔ ፍርኃት አለኝ፣ ሥጋት አለኝ!
  • የምን ሥጋት?
  • አመራሩ ልቡ ሸፍቷል የት ቦታ እንደቆመ አይታወቅም። ይኼ አስፈርቶኛል።
  • ስለዚህ?
  • ሥጋት ስላለኝ ነው ፈጥኜ እስከ ወረዳ ያለውን አመራር በጥቅማ ጥቅም ለመያዝ የወሰንኩት።
  • እንደዚያ ነው?
  • አዎ። ፍርኃት ስላለኝ ነው። ሥጋት አለኝ።
  • እንደዚያ ከሆነ ገብቶታል ማለት ነው።
  • ምኑ?
  • ፕሮጀክቱ።
  • የቱ ፕሮጀክት?
  • የ90 ቀን!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ አልባ በማድረግ ታሪክ አይሠራም

በኢተፋ ቀጀላ​​  ከዛሬ ሃምሳ ዓመት ወዲህ ከተፈጠሩት የኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ከኢጭአት በስተቀር፣...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...

ጉራጌን በክላስተር ለመጨፍለቅ የሚደረገውን ጥረት እንደሚቃወም ጎጎት ፓርቲ አስታወቀ

ለጉራጌ ሕዝብ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበር እንደሚታገል የሚናገረው አዲሱ...

‹‹ኢኮኖሚው ላይ የሚታዩ ውጫዊ ጫናዎችን ለመቀልበስ የፖሊሲ ሪፎርሞች ያስፈልጋሉ›› ዓለም ባንክ

በዓለም ደረጃ ከተፈጠረው የኢኮኖሚ አለመረጋጋት ጋር በተገናኘ፣ በኢትዮጵያ ውጫዊ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

‹‹ከኦነግ ሸኔ ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት አለን›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ

መንግሥት ከ‹‹ኦነግ ሸኔ››ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት...

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣን በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለመመካከር በሚኒስትሩ ቢሮ ተገኝተው ውይይታቸውን ጀምረዋል]

ክቡር ሚኒስትር ባላንጣዎቻችን የእኛኑ ስልት መጠቀም የጀመሩ ይመስላል። እንዴት? ምን አዲስ ነገር ተፈጠረ? እስከዛሬ እኛ የምንሰጣቸውን አጀንዳ ተቀባይ ነበሩ። በዚህም በውስጣቸው ልዩነትንና አለመግባባትን መትከል ችለን ነበር። አሁን...