Tuesday, October 3, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየፌዴራል ፍርድ ቤቶች ክርክር ተጠናቆ በከተማ ነክ ፍርድ ቤት ይግባኝ የተጠየቀባቸው ፓስተር...

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ክርክር ተጠናቆ በከተማ ነክ ፍርድ ቤት ይግባኝ የተጠየቀባቸው ፓስተር ቢኒያም ሽታዬ ተፈቱ

ቀን:

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተፈጥሮ በነበረው የሲኖዶስ ግልበጣ ሙከራ ጋር በተያያዘ፣ አጋጣሚውን በመጠቀም ሁከት ለመፍጠርና ሌላ አጀንዳ  ከሌሎች ፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር በመመሳጠር ሲንቀሳቀሱ ተገኝተዋል በሚል ተጠርጥረው የታሰሩት ፓስተር ቢኒያም ሽታዬ፣ ከፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ እስከ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ደርሰው ዋስትና ቢፈቀድላቸውም፣ ሳይፈቱ ከርመው በከተማ ሰበር ሰሚች ችሎት ይግባኝ ከተጠየቀባቸው በኋላ፣ ትናንት ምሽት ከ12፡00 ሰዓት በኋላ ፖሊስ ለቋቸዋል፡፡

ፓስተሩ ከእስር የተፈቱት ጠበቆቻቸው መጀመርያ የክስ መዝገብ ተከፍቶባቸው ለነበረው የፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት አቤቱታ አቅርበው፣ ፍርድ ቤቱ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ስለሁኔታው ዛሬ ረቡዕ የካቲት 29 ቀን 2015 ዓ.ም. ቀርቦ እንዲያስረዳ ትዕዛዝ ከተሰጠ በኋላ ነው፡፡

ጠበቆቻቸው ይግባኝ አቅርበው የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ለምን እንደማይከበር ሲጠይቁ፣ የአራዳ ፖሊስ ለንፋስ ስልክ ፖሊስ አሳልፎ እንደሰጣቸው ቢያስረዳም፣ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ፖሊስ እንደለቀቃቸውና የልደታ ፖሊስ በሌላ ወንጀል ጠርጥሯቸው እንዳሰራቸው ሲያስረዳ፣ ጠበቆች ደንበኛቸው (ፓስተር ቢኒያም) የትኛውም ፖሊስ ጣቢያ ቢያስራቸውም፣ የሁሉም ፖሊስ ጣቢያዎች ኃላፊ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በመሆኑ፣ ፍርድ ቤቱ እንዲጠይቅላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡

ፍርድ ቤቱም የኮሚሽኑ ኃላፊ ከንጋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ቀርቦ እንዲያስረዳ ቀጠሮ ሰጥቶ እያለ፣ ምሽት ላይ ፖሊስ እንደለቀቃቸው ጠበቃቸው አቶ ብሩክ ተፈራ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡

ፓስተር ቢኒያም የካቲት 17 ቀን 2015 ዓ.ም. የፌዴራል መጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት በ5,000 ብር ዋስ እንዲለቀቁ ትዕዛዝ መስጠቱን፣ ፖሊስ ይግባኝ ቢልም ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትዕዛዙን ማፅናቱንና ወደ ሰበር ቢሄድም የሕግ ጥሰት እንደሌለ ገልጾ፣ መዝገቡን ከዘጋው በኋላ ፖሊስ ጉዳዩን ወደ ከተማ ፍርድ ቤት መውሰዱን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተመድንና ዓለም አቀፋዊ ሕግን ከእነ አሜሪካ አድራጊ ፈጣሪነት እናድን!

በገነት ዓለሙ በእኔ የተማሪነት፣ የመጀመርያ ደረጃ ተማሪነት ጊዜ፣ የመዝሙር ትምህርት...

የሰላም ዕጦትና የኢኮኖሚው መንገራገጭ አንድምታ

በንጉሥ ወዳጅነው ፍራንክ ቲስትልዌይት የተባሉ አሜሪካዊ ጸሐፊ ‹‹The Great Experiment...

ድህነት የሀብት ዕጦት ሳይሆን ያለውን በአግባቡ ለመጠቀም አለመቻል ነው

በአንድነት ኃይሉ ድህነት ላይ አልተግባባንም፡፡ ብንግባባ ኖሮ ትናንትም ምክንያት ዛሬም...