መቄዶንያ የአረጋውያንና አእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል እያስገነባ ለሚገኘው አዲሱ ህንጻ በር እና መስኮት ማስገጠሚያ ድጋፍ እየተሰባሰበ ይገኛል።
በአጠቃላይ የሚገጠሙት በሮች ቁጥር 888 እንዲሁም የመስኮቶቹ ደግሞ 739 ሲሆን የአንድ በር ዋጋ 106ሺህ ብር እንዲሁም የአንድ መስኮት ዋጋ 80ሺህ ብር ነው።
ለበር እና መስኮት ማስገጠሚያ ድጋፉ በተለያዩ አማራጮች እየተደረገ ሲሆን፤ ድጋፍ ለማድረግ –
• በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ በኦሮሚያ ኀብረት ሥራ ባንክ፣ በዳሸን ባንክ፣ በአቢሲንያ ባንክ እና በአባይ ባንክ – ለሁሉም በተመሳሳይ የሂሳብ ቁጥር 8161 ላይ
• ጎ ፈንድ ሚ (GoFundMe) – Mekedonia Charity Homes: https://www.gofundme.com/f/Mekedonia-Charity-help-build-home-for-the-homeless
• Cash App: 240-840-6256
• Zelle: 240-840-6256
• WEGEN FUND : https://www.wegenfund.com/causes/
መቄዶንያ በማዕከሉ ላሉ ሰዎች ሁሉንም መሰረታዊ አገልግሎቶች ማለትም ምግብ፣ አልባሳት፣ መጠለያ፣ ንፅህና መጠበቂያ፣ ህክምና፣ ትምህርት እና ሌሎች መሰል አገልግሎቶችን በመስጠት የአረጋዊያንን እና የአእምሮ እክል ያለባቸውን ህይወት በመርዳት ላይ ያተኮረ ድርጅት እንደሆነ ይታወቃል።