Friday, March 24, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅፀሐይን እንዲህ አላት

ፀሐይን እንዲህ አላት

ቀን:

‹‹ዛራቱስትራ የሠላሳ ዓመት ጐልማሳ በሆነ ጊዜ አገሩንና የአገሩንም ወንዞች ትቶ ወደ ተራራ ሄደ፡፡ በዚያም የገዛ ራሱን መንፈስና ብቸኝነቱን በመደሰት ምንም ስጋት ሳይሰማው አሥር ዓመት ኖረ፡፡ በመጨረሻ ልቡ ተመለሰ፡፡ አንድ ቀን ማለዳ ተነሣ፡፡ በፀሐይዋ ፊለፊት ቆሞ እንዲህ ሲል ተናገራት፡፡

ትልቅ ኮከብ ሆይ፤ ብርሃንሽን የምታድያቸው ባይኖሩሽ ኖሮ ደስታሽ ምን ይሆን ነበር፡፡ አሥር ዓመት ሙሉ በየዕለቱ እስከዋሻዬ ድረስ ትመጭ ነበር፡፡ እኔና አብረውኝ ያሉት ንስርና እባብ ባንኖር ኖሮ ስለብርሃንሽና ስለጉዞሽ ሐሳብ ይገባሽ ነበር፡፡ ግን እኛ በየጧቱ እንጠባበቅሽ ነበር፡፡ ተትረፍርፎ ካንቺ የሚፈሰውን ወሰድን፤ ስለሱም መረቅንሽ፡፡

እነሆ፤ ስለጥበቤ ሐሳብ ገባኝ፤ ብዙ ማር እንዳከማቸች ንብ ለመውሰድ የተዘረጉ እጆች አስፈለጉኝ፡፡ ወዲያ ለመስጠትና ለማደል እፈልጋለሁ፡፡ በሰዎች መካከል ያሉት ጠቢባን በሞኝነታቸው፤ ድሆችም በሀብታቸው እስኪደሰቱ ድረስ፡፡ በዚህ ዓላማ ምክንያት አሁን ቁልቁል መውረድ አለብኝ፡፡ ሁልጊዜ በየምሽቱ እንደምታደርጊው፣ በባሕሩ ማዶ አልፈሽ በታችኛው ዓለም ላሉት ብርሃን ለመስጠት እንደምትሄጅ፣ እጅግ ባለፀጋዋ ኮከብ ሆይ፡፡

እኔም እንዳንቺ ወደታች ‹‹መጥለቅ›› አለብኝ፤ የምወርድላቸው ሰዎች እንደሚሉት፡፡ ከመጠን በላይ የሆነውን ደስታ እንኳ ያለቅናት የምታይ፣ ሰላምን የተመላሽ ዓይን ሆይ፣ እንግዲህ መርቂኝ፡፡

ተርፎ ለመፍሰስ የሚፈልገውን ዋንጫ መርቂ፣ ውኃው ከሱ እንደ ወርቅ ይፈስ ዘንድ፤ የደስታሽንም ማንፀባረቅ (ሪፍሌክሽን) ወደመላው ዓለም ይሸከምልሽ ዘንድ፡፡ እነሆ ይህ ዋንጫ እንደገና ባዶ ለመሆን ፈለገ፤ ዘራቱስትራም ዳግመኛ ሰው ለመሆን ተመኘ፡፡

እጓለ ገብረ ዮሐንስ ‹‹የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ›› (1956)

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...