Thursday, March 23, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
- Advertisement -

ፌርማታ ፅሁፎች

‹‹የሀገራችንን ገመና የሚያውቁት መሰለኝ››

ትኩስ ፅሁፎች

‹‹ደስ ያለህ ትመስላለህሳ!›› አለው ሰውየው ተላላኪው ማፍቀሯን ለመግለጽ ወኔ እንደከዳት ዓይናፋር ልጃገረድ እየተሽኮረመመ፡፡

‹‹ትንሽ ሎተሪ ቀንቶኝ ነበር››

‹‹ዕድለኛ ነህ ጃል ለመሆኑ ምን ያህል ነበር?

ተላላኪው ጥቂት ካመነታ በኋላ ‹‹አንድ መቶ ሴዲ ነው›› አለ፡፡

‹‹ብዙ አይደለማ!›› ሰውዬው እየሳቀ፡፡

‹‹ብዙ እንዳልሆነ አውቃለሁ ግን ብዙ ሰው እንደሚያስቸግረኝ ወይም እጅ እጄን እንደሚያይ ደግሞ እገምታለሁ››

‹‹እሱ ሳይታለም የተፈታ ነው››

‹‹እሱ እንኳ ማንም ሊያውቅ አይችልም››

‹‹እንዴት? ትኬቱን በቅጽል ስም ነበር እንዴ የቆረጥኸው?››

ደስታህን ያዝልቅልህ አለው ሰውየው፡፡

‹‹አመሰግናለሁ ደስታዬ ግን ከስጋት ነፃ አይደለም አለ ተላላኪው ፊቱን ኮስኩሶ፡፡

‹‹መተተኛ ምናምን?››

‹‹አይ ነገሩ ወዲህ ነው የሀገራችንን ገመና የሚያውቁት መሰለኝ››

‹‹አዎን እንጂ እንዴታ!››

‹‹ሁሉም ሰው የጋና ሎተሪ ውስጡን ለቄስ ነው ይላል››

‹‹ስጋትህ ገንዘቤን አላገኝ ይሆናል የሚል መሰለኝ››

‹‹እንዴታ! ጌታዬ አምና ከአምስት መቶ ሴዲ በላይ ወጥቶላቸው እስካሁን ድረስ ቀይ ሳንቲም ያላሸተቱ ደንበኞች እንዳሉ አውቃለሁ፡፡››

‹‹ለፖሊስ ወይም ለፍትሕ አካላት አላመለከቱም ነበር?››

‹‹ያሾፋሉ መሰለኝ›› አለ ተላላኪው በምሬት ቅላፄ

‹‹አባቱ ዳኛ ልጁ ቀማኛ›› አሉ ለፖሊስ ማመልከት ማለት እኮ ለበለጠ ወጭ መዳረግ ማለት ነው?››

‹‹አሁን ታዲያ ምን ተሻለ?››

‹‹እዚያው ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ውስጥ ከዕጣዬ ውስጥ የተወሰነውን ጎርሶ ቀሪው የሚያስለቅቅልኝ ባለሥልጣን አላጣም የሚል ተስፋ አለኝ፡፡ ከማለቱ ፊቱ የተቃጠለ ቅጠል መሰለ፡፡

‹‹የአንድን የመንግሥት ባለሥልጣን በጉቦ ቅሌት ማስገኘት አይሆንብህም›› አለው ሰውየው በስላቅ፡፡

‹‹ጌታዬ ምን ነካብኝ ምድሪቱ’ኮ ጋና ናት ይህን ለርስዎ መንገር ለቀባሪ ማርዳት ነው›› እያለ ከቢሮው ለመውጣት ተነሣ፡፡

  • መላክነህ መንግስቱ ‹‹አልነጋም ገና ነው››
- Advertisement -
- Advertisement -

ተጨማሪ ለማንበብ

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች