ተግባራዊ ጥበብን የሚያጎሉ በርካታ ምሳሌያዊ አነጋገሮች የአስተዋይነትንና የአርቆ ተመልካችነትን አስፈላጊነት በጥሩ ሁኔታ ይገልጻሉ። የሚያደርጋቸው ነገሮች ምን መዘዝ እንደሚያስከትሉ ሳያመዛዝን አንድ ነገር ውስጥ ዘው ብሎ የሚገባ ግድየለሽ ሰው ከሚከተለው ተረት ጥሩ ምክር ያገኛል። “እባቡን ከማስቆጣትህ በፊት መውጫህን አሰናዳ።” መጥፎ አዝማሚያ የሚታይበት ልጅ ያለው ወላጅ የሚከተለውን ተረት ልብ ማለት ያስፈልገዋል።
“የሚያድግ ቅርንጫፍ ዓይንህን ሊወጋ ከተቃረበ ንቀለው እንጂ አትመልምለው።” አዎን፣ ማንኛውም መጥፎ ባሕርይ ገና በእምቡጥነቱ መቆረጥ ወይም መነቀል ይኖርበታል እንጂ አቆጥቁጦ ችግር እስኪፈጥር ድረስ መታለፍ አይኖርበትም።
- (ንቁ!—2003)