Friday, March 31, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ ስለፖለቲካ ማርኬት ፕሌስ ጽንሰ ሐሳብ አጥንተው ከፍተኛ አመራሮችን ሲያሠለጥኑ ቢሰነብቱም ዛሬ ከባለቤታቸው የተነሳውን ጥያቄ ለመመለስ ተቸግረዋል]

  • እኔ ምልህ ክቡር ሚኒስትር?
  • ክቡር ሚኒስትር ካልሽኝ ችግር አለ ማለት ነው።
  • ችግርማ አለ።
  • እሺ … እኔ ምልህ ያልሽው ለምን ነበር?
  • ልጠይቅህ ነዋ።
  • ምን?
  • ከጥቂት ሳምንታት በፊት ስትሰብኩት የነበረው ነገር የውሸት ነው ማለት ነው?
  • ምን ሰበክን?
  • በመጀመሪያ የፓርቲ አባሎቻችሁን ቀጥሎ ማኅበረሰቡን ስለፖለቲካ ማርኬት ፕሌስ ወይም ስለፖለቲካ ገበያ ስትግቱ አልነበረም እንዴ?
  • አዎ፣ ስለአገሪቱ የፖለቲካ ገበያ መበላሸት ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ አሁንም እየሠራን ነው።
  • ግን እናንተ ራሳችሁ ስለጽንሰ ሐሳቡ ግንዛቤ አላችሁ?
  • እንዴት? ምን ዓይነት ጥያቄ ነው?
  • መንግሥት ራሱ የፖለቲካ ሸቀጥ ይዞ ገበያ መውጣቱን ስመለከት ጊዜ ግራ ገብቶኝ ነዋ፡፡
  • መንግሥት እንዴት እንደዚህ ያደርጋል? ጽንሰ ሐሳቡ አልገባሽም ማለት ነው?
  • የፖለቲካ ገበያ ማለት የፖለቲካ ሥልጣን ለመያዝ ወይም የመንግሥትን ሥልጣን ለማፅናት ለገበያ የሚያቀርብ ሸቀጥ አይደለም እንዴ?
  • ትክክል ነሽ፣ አንዱ መገለጫው እሱ ነው።
  • ሥልጣንን ለማፅናት የብሔር ወይም የሃይማኖት ድጋፍ ለማግኘት መትጋት የፖለቲካ ሸቀጥ አይደለም?
  • ነው እንጂ፣ እንዲያውም አደገኛው እሱ ነው።
  • የፖለቲካ ገበያው መበላሸት የሚያስከትለው ውጤት ተቋምን፣ ቀጥሎም አገርን የማፍረስ አደጋ ያስከትላል ስትሉም ሰምቻለሁ አይደል?
  • ትክልል ነሽ? ይህ አዝማሚያ አደገኛ ነው ያልንበት ምክንያት አገር ስለሚያፈርስ ነው።
  • ታዲያ አገር በሆነችው ቤተ ክርስቲያን ላይ ለምን መዝመት ፈለጋችሁ?
  • እሱ እንኳን ከዚህ ጋር አይገናኝም።
  • እንዴት አይገናኝም?
  • የሃይማኖት ጉዳይ ስለሆነ።
  • የሃይማኖት ጉዳይ ብቻ እንዳልሆነማ ግልጽ ነው።
  • እንዴት?
  • ነገሩ የሲኖዶሱን አብላጫ ለመቆጣጠር ወይም አገር ናት ያላችኋትን ተቋም ለመከፋፈል የሚደረግ ጥረት ነው።
  • ለምን ብለን እንደዚያ እናደርጋለን?
  • ለማፅናት ፈልጋችሁ ይመስለኛል።
  • ምን ለማፅናት?
  • ሥልጣናችሁን፡፡
  • በፍፁም፣ ተሳስተሻል፡፡
  • ታዲያ ለምን ችግሩን ለመፍታት ሰነፋችሁ?
  • ሰንፈን አይደለም።
  • እና ምን ሆናችሁ ነው?
  • መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባት ስለማይችል ነው።
  • ታዲያ ለምን እናንተ ገባችሁ?
  • አልገባንም?
  • የቤተ ክርስቲያን ተቋማትን እየሰበሩ መቆጣጠር የጀመሩትን እያያችሁ ዝም ማለታችሁ እኮ ያው ነው።
  • ያው ነው ማለት?
  • ጣልቃ መግባት ነው፡፡
  • በፍፁም! የመንግሥት ፍላጎት ራሳቸው ተነጋግረው ልዩነታቸውን እንዲፈቱት ብቻ ነው።
  • የአዲስ አበባ ባለአደራ አስተዳደር በሚል ተጀምሮ የነበረውን እንቅስቃሴ ታስታውሳለህ?
  • አዎ፣ እሱን በምን አስታወሽው?
  • በወቅቱ የነበረው ጭንቀታችሁ ትዝ ብሎኝ ነው።
  • በአንድ ከተማ ላይ ሁለት አስዳደር ለመፍጠር መሞከር ትክልል አይደለም፣ በዚያ ላይ አካሄዱ አስፈሪ ነበር።
  • ቢሆንም ከማሰር ይልቅ በውይይት ብትፈቱት ይሻል ነበር።
  • እንዴት አድርገን ነው ከእነሱ ጋር የምንወያየው?
  • አሁን የቤተ ክርስቲያን ችግር በውይይት ይፈታል እንዳልከው።
  • እሱ ሌላ! ያ ሌላ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

አሜሪካ ሕወሓትን በማሳመንና በመጫን በሰላም ሒደቱ ትልቅ ሚና መጫወቷን የኢትዮጵያ ዋና ተደራዳሪ አስታወቁ

የተመድና የአውሮፓ ኅብረት አበርክቶ አሉታዊ እንደነበር ጠቁመዋል በመንግሥትና በሕወሓት መካከል...

ሥራ ከጀመረ አራተኛ ወሩን የያዘው ፀሐይ ባንክ ካፒታሉን ወደ አምስት ቢሊዮን ብር ለማሳደግ ወሰነ

በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የግል ባንኮች በተለየ ሁኔታ በ373 ባለአክሲዮኖች...

ጎህ ቤቶች ባንክ ወደ ቤት ልማት ለመግባት ብሔራዊ ባንክን ፈቃድ ጠየቀ

በስምንት ወራት ውስጥ 7.9 ሚሊዮን ብር ማትረፉን አስታውቋል ኢትዮጵያ ውስጥ...

ኢትዮጵያ በ2023 የሚኖራት የውጭ ምንዛሪ ክምችት ለ18 ቀናት ግዢ መፈጸሚያ ብቻ እንደሚሆን አይኤምኤፍ ተነበየ

ኢትዮጵያ በ2023 የሚኖራት የውጭ ምንዛሪ ክምችት ለ0.6 ወር ወይም...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...

አይ የእኛ ነገር!

የዛሬው ጉዞ ከጀሞ ወደ ፒያሳ ነው፡፡ መንገዱ ለሥራ በሚጣደፉ፣...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ አባላቱ የተከበሩ ተብለው የሚጠሩት በምክንያት አይደለም እንዴ? ትክክል ነው። ምክንያቱም፣ ምክር ቤቱ ትልቁ የሥልጣን አካል ነው፣...

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...