Saturday, December 2, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ ወደ ቢሯቸው እንደገቡ የፖለቲካ አማካሪያቸው ስለ ሰሜኑ ግጭት የሰላም ስምምነት አተገባበር ማብራሪያ ለመጠየቅ ገባ]

  • ክቡር ሚኒስትር ጥሰውታል?
  • እንዴ? እስኪ ተረጋጋ ምንድነው? መጀመርያ ሰላምታ አይቀድምም?
  • ይቅርታ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምን ገጥሞህ ነው?
  • ስምምነቱን ጥሰውታል ክቡር ሚኒስትር?
  • ኧረ ተውው ተረጋጋ፡፡
  • እሺ ክቡር ሚኒስትር ይቅርታ… ደንቆኝ እኮ ነው።
  • ስምምነቱን እንደጣሱ በምን ተረዳህ?
  • ክቡር ሚኒስትር የፌዴራል መንግሥት ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲመሠርት ተስማምተው ሳሱ እነሱ ግን ከዚህ የሚቃረን ተግባር ሰሞኑን ፈጽመዋል።
  • ምን አደረጉ?
  • እንደኛ አዲስ የካቢኔ አደረጃጀት ላይ ውሳኔ አሳልፈዋል።
  • ሁለተኛውስ?
  • በስምምነቱ መሠረት የክልሉ ምክር ቤት መበተን ሲኖርበት ሌላ ነገር ተወስኖል።
  • ምን ተወሰነ?
  • የክልሉ ምክር ቤት ሕግ የማውጣት ሥልጣኑን ለክልሉ ሥራ አስፈጻሚ አሳልፎ ሰጥቷል።
  • አየህ ተረጋጋ ያልኩህ ለዚህ ነበር።
  • ለምን? እንዴት?
  • የክልሉ ምክር ቤት አዲስ የሥራ አስፈጸሚ መዋቅር ላይ ከወሰነ በኋላ ሕግ የማውጣት ሥልጣኑን ለሥራ አስፈጸሚው አሳልፎ ሰጠ ማለት ትርጉሙ ሌላ ነው።
  • አዲስ የሥራ አስፈጻሚ መዋቅር ላይ ሲወሰን የሚቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር ተቀበለ ማለት ነው።
  • እህ… እሺ እሱ እንደዛ ይሁን ሕግ የማውጣት ሥልጣኑን ለምን አሳልፎ ሰጠ?
  • ሕግ የማውጣት ሥልጣኑን ለሥራ አስፈጻሚው አሳልፎ ሰጠ ማለት ደግሞ ምን መሰለህ?
  • ምን ማለት ነው?
  • የክልሉ ምክር ቤት ፈረሰ ማለት ነው!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከደኅንነት ጉዳዮች አማካሪያቸው ጋር ስለ ወቅታዊ ጉዳች እየተወያዩ ነው]

  • በድርጅት ደረጃ የተወሰነው ጉዳይ አፈጻጸም በምን ደረጃ ላይ ነው?
  • የትኛውን ማለትዎ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • በቅርቡ ስለ ፖለቲካ ማርኬት ፕሌስ ተወያይተን ውሳኔ ማሳለፋችንን ዘነጋኸው? ወይስ አንተም…
  • እኔ ምን ክቡር ሚኒስትር?
  • ተጠልፈህ እንዳይሆን ብዬ ነው።
  • ማን ይጠልፈኛል ብለው ነው?
  • የፖለቲካ ነጋዴዎቹ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እየቀለዱ መሆን አለበት?
  • ግራ ሲገባኝ እኮ ነው።
  • ግራ የገባዎት ምንድነው?
  • ማንን ማመን እንዳለብኝ።
  • ክቡር ሚኒስትር በእኔ መሥጋት የለበዎትም። የውሳኔዎቹን የእስካሁን አፈጻጸም በተመለከተ ግን ማለት የምፈልገው ነገር አለ።
  • ምንድነው ቀጥል።
  • ክቡር ሚኒስትር በድርጅትም ሆነ በመንግሥት ደረጃ ለይተን ያወጣነው የፖለቲካ ንግድ መንሰራፋት በንድፈ ሐሳብ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በተግባርም የብሔራዊ ደኅንነታችን ዋና ፈተና መሆኑን አረጋግጠናል።
  • እንዴት?
  • እነዚህን የፖለቲካ ንግድ ተዋናዮች ከመዋቅራችን ቆርጦ የማውጣት መጠነኛ እንቅስቃሴ ብዙ ነገር እያሳየን ነው።
  • ምን አስተዋላችሁ?
  • ዋናው ነገር ይህ ችግር የብሔራዊ ደኅንነታችን ፈተና መሆኑን ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ተዋናዮቹ ላይ መውሰድ የጀመርነው ዕርምጃ አደገኛ ምልክቶችን እያሳየን ነው።
  • አደገኛ ማለት?
  • ክቡር ሚኒስትር አንዱ ቦታ ዕርምጃ ለመውሰድ ስንሞክር የተፈጠረው ኔትወርክ በሌላ ቦታ ግጭት እየቀሰቀሰ አገሪቱን የማፈረስ አደጋ እየደቀነ ነው።
  • እስኪ ሁኔታውን በዝርዝር አስረዳኝ?
  • ክቡር ሚኒስትር ለምሳሌ ሰሞኑን ቤተ ክርስቲያን ላይ የተሞከረውን መውሰድ እንችላለን። ይህ ጉዳይ በቀጥታ የእነዚሁ የፖለቲካ ንግድ ተዋናዮች ኔትወርክ መሆኑን ደርሰንበታል።
  • እህ…
  • ዕርምጃው የክልል አመራሮችንም እንደሚያካትት የገመቱ ደግሞ አቅማቸውን ለማሳየት እየሞከሩ ነው።
  • እንዴት?
  • ዕርምጃው ገና ወደ ክልል መዋቅሮች ሳይደርስ በአጣዬ ግጭት በመቀስቀስ ቢነኩ ምን ሊፈጠር እንደሚችል እያሳዩን ነው።
  • ምን ሊፈጠር ይችላል?
  • የእነሱ ሥሌት የብሔር ግጭት መፍጠር ነው።
  • እህ….
  • በአዲስ አበባ አስተዳደር በመሬት ሥርቆት የጠረጠርናቸው ደግሞ መረጃ የማውደም ተግባር ፈጽመዋል።
  • ምን አደረጉ?
  • ግንባታው ተጠናቆ ሊመረቅ ቀጠሮ የተያዘለት የክፍለ ከተማው የመረጃ ማዕከልን በእሳት አጋይተውታል።
  • ዘግይተናል ማለት ነው?
  • ምን አሉኝ?
  • በዚህ ደረጃና ጥልቀት እስኪንሰራፉ አለመንቃታችን ያናዳድል።
  • አሁን እሱ አይጠቅምም ክቡር ሚኒስትር።
  • ምኑ?
  • መናደድ።
  • እና ምንድነው የሚጠቅመው?
  • መፍትሔውን ማለም!
   
 
     

 

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...

ሀብቱንና ትርፉን እያሳደገ የቀጠለው አዋሽ ባንክ

አዋሽ ባንክ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ዋና መሥሪያ ቤት...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸማቸውን ለተከበረው ምክር ቤት ካቀረቡ በኋላ ከምክር ቤቱ አባላት የሚነሱ ጥያቄዎችን እየተቀበሉ ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው]

ክቡር ሚኒስትር መንግሥት ለሕዝብ ይፋ ያደረገው ነገር ከምን እንደደረሰ ቢያብራሩልን? ምንድነው ይፋ ያደረገው? ጥያቄውን ትንሽ ቢያብራሩት? ከአራት ዓመት በፊት በኦጋዴን አካባቢ ነዳጅ መገኘቱን ለሕዝብ በቴሌቪዥን አብስሮ...

[ክቡር ሚኒስትሩ አንድ የካቢኔና የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ አባል የሆኑ ከፍተኛ አመራር የሚያቀርቡትን ቅሬታ እያደመጡ ነው] 

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር በእጅጉ ስላሳሰበኝ ነው በአካል አግኝቼ ላነጋግርዎት የፈለግኩት። ጥሩ አደረግህ፣ ምን አሳሳቢ ነገር ገጥሞህ ነው? ክቡር ሚኒስትር ተወያይተንና ተግባብተን ያስቀመጥናቸው አቅጣጫዎች፣ በተለይም...

[ጉባዔው በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ክቡር ሚኒስትሩን ለመጠየቅና ምላሽና ማብራሪያቸውን ለማድመጥ ተሰብስቧል። የጉባዔው አባላትም ማብራሪያ የሚሹ ጥያቄዎቻቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር፣ ይህ ጉባዔ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ለመስጠት በመካከላችን ስለተገኙ አመሰግናለሁ። ክቡር ሚኒስትር፣ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት የብሪክስ አባል እንድትሆን የሰጡት በሳል አመራር የሚደነቅ ነው። አገራችን...