Thursday, March 23, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ኪንና ባህልየዓድዋ ድል በዓልን በዓድዋ ዜሮ ኪሎ ሜትር ሙዚየም ለማክበር ታሰበ

የዓድዋ ድል በዓልን በዓድዋ ዜሮ ኪሎ ሜትር ሙዚየም ለማክበር ታሰበ

ቀን:

ኢትዮጵያ ከ127 ዓመታት በፊት በዓድዋ በወራሪው የጣሊያን ሠራዊት ላይ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም. ድል የተቀዳጀችበት በዓል፣ እየተገባደደ ባለው የዓድዋ ዜሮ ኪሎ ሜትር ሙዚየም ለማክበር መታሰቡን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትልልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡

የጽሕፈት ቤቱ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አዲስ አረጋይ ታኅሣሥ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. እንደገለጹት፣ የዓድዋ ድል በሚዘክርበት በዚህ ፕሮጀክት የዘንድሮው ክብረ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ ከፍ ባለ ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ለማክበር እንዲቻል፣ በሙዚየሙ ውስጥ ተካቶ ያለውን የበዓሉን ማክበሪያ ሥፍራ ለማጠናቀቅ ቅድሚያ ተሰጥቶት እየተሠራ ነው፡፡

የዓድዋ ሙዚየም ዜሮ ኪሎ ሜትር ፕሮጀክት ግንባታ ሲጠናቀቅ ከ2,000 እስከ 4,000 ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል የመሰብሰቢያ አዳራሽ፣ የሕዝብ ቤተ መጻሕፍት፣ የተለያዩ ቢሮዎች፣ ካፍቴሪያና የመሳሰሉትን አገልግሎቶችን የሚሰጡ ክፍሎች፣ የቤት ውስጥ ስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች፣ የአውቶቡስና የታክሲ መናኸርያ፣ እንዲሁም ከሕንፃው ውጪ የቴአትርና የዓውደ ርዕይ ማሳያ ቦታዎች እንደሚኖሩት ተገልጿል፡፡
4.6 ቢሊዮን ብር የተበጀተለትና ግንባታው በመስከረም 2012 ዓ.ም. የተጀመረውን ይህን ፕሮጀክት በተቋራጭነት ቻይና ጂያንግሱ ኢንተርናሽናል የተሰኘው ኩባንያና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትልልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽሕፈት ቤት በባለቤትነት እያከናወኑት የሚገኝ ነው።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...