Tuesday, March 28, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅ‹‹ሽሮሜዳ ብቻ ናት የሚያቀነቅኑ ላሞች ያሉባት››

‹‹ሽሮሜዳ ብቻ ናት የሚያቀነቅኑ ላሞች ያሉባት››

ቀን:

«…….. ሽሮሜዳ አማረም አላማረም ማንም በልቶ ጠግቦ የሚያድርባት ሥፍራ ናት፡፡ ልጆቻችን የረጉ፣ በሳቅ በጨዋታ ነፍሳቸውን የቀለለችና የተኳለች ናት፡፡ አያድርገውና ቢያደናቅፋቸው መሬት አይነኩም፡፡ መሬት ነክተው እንዳይጎዱ ከሚንሳፈፉበት አየር ላይ በወገናቸው በፍጥነት ይለቀማሉ። እዩ እግሮቼንና ክንዶቼን። ሺሕ ጊዜ አደናቅፎኛል፣ ሺሕ ጊዜም ወድቄአለሁ፡፡ ምንም ጠባሳ ግን የለብኝም። እዳሪያችን ድስት፣ መሶብና ማዕድ ነው። የሰውን ተውኝና ባለቤት የሌላቸው ለቅልውጥና የመጡ የሌላ ሰፈር ውሾች እንኳን እዛ እዛ ብለው ቀራርመው የሚመሰጡበት ቁራጭ ሥጋ፣ መቅኒ የለጎመ አጥንት አያጡም።

ንቦቻችን ፍጡር ናቸውና ክብር አላቸው፡፡ ይኼም ንቁ አድርጎአቸዋል። ጌጥ ስለሚወዱና ኪነጥበብ ስለሚያደንቁ በዓይን ማየት የሚያዳግት ቁንዳላቸውን ለማበጠሪያ ክንፎቻቸው ሥር ከሰንደል እንጨት የተበጀች ደቃቃ ሚዶ ይዘው ይበራሉ። ከዚያም አልፎ አይኖቻቸውንም ይኳላሉ፡፡ በየቦታው ሲንዛዙ ወለላ ማጠራቀሚያ ወርቅማ ሙዳዮች በጀርባቸው አዝለው ነው፡፡ ጣፋጭነታችን በአንደበታችን፣ በዘፈናችንና በሽፈነን ቆዳችን ላይ አለ። ልብሶቻችን ለአንድ ሰዓት ያህል እውጭ ቢሰጡ፣ ከላያቸው የሚወርደው ዮጵ የመሰለ ማር ነው፡፡ ጥርሶቻችን ነጫጮች ናቸው። እኔን እዩ (እኝ)፡፡ ከብቶቻችን የሚግጡት የባቄላና የአተር ደን ነው (አለነገር ‹ሽሮሜዳ› ተባለ መሰላችሁ?) ቅቤያችን ያለ አላቢ ከላሞቻችን ግት በራሱ ፈቃድ እተንዠረዠረ ይወጣል። ጀምበር ስታዘቀዝቅ፣ ብዙ ‹እምቧ› ብትሰሙ የሰፈራችን ጥገቶች ‹ወተታችንን ውሰዱ› እያሉ ሲለማመጡን ነው።

ለታሪክ የሚቀመጥ አንድ ነገር እንካችሁ። በዚህች ዓለም ላይ ሽሮሜዳ ብቻ ናት የሚያቀነቅኑ ላሞች ያሉባት፡፡ ይኼ ቀጥሎ የምትሰሙትን ‹እምቧ በይ ላሚቱ› የተባለውን የሙሉቀን መለሰን ዘፈን መጀመሪያ ያንጎራጎረችው ‹ቡራቡሪት› የተባለች የሽሮሜዳ ላም ናት…» (አንድ የሽሮሜዳ ወጣት ስለ ሽሮሜዳ ሰፈር በኢትዮጵያ ሬድዮ መዝናኛ ፕሮግራም ላይ ካነበበው የተቀነጨበ 1963 ዓ.ም.)

  • አዳም ረታ ‹‹መረቅ››
spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

‹‹ከኦነግ ሸኔ ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት አለን›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ

መንግሥት ከ‹‹ኦነግ ሸኔ››ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት...

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...