እነሆ ሁለት ቂሳ ባጭሩ አብዱልቃዱር ጅላሊ ከባግዳድ ነው የመጡት ይባላል፡፡ እሮብ በስማቸው የሚከበርላቸው፡፡
ለአያሌ ዓመታት ሲያገለግሉዋቸው የኖሩትን ሁለት ተከታዮቻቸውን የሚያሰናብቱበት ጊዜ ደረሰ፡፡ የትኛውን ወዴት እንደሚልኩትና እዚያስ ምን እየሰራህ ትተዳደራለህ እንደሚሉት ለማወቅ በሌላ አባባልም የሁለቱን ዋጋ ወይም ክብደት ለመመዘን እንዲህ አደረጉ፡፡ ለሁለቱም አንድ ዶሮ ሰጡዋቸውና “ለየብቻችሁ ሂዱና ዶሮዋል እኔ በሌለሁበት ስፍራ አርዳችሁ አምጡልኝ አሉዋቸው፡፡ ተቀብለው ቢላ ቢላቸውን ይዘው ሄዱ፡፡
አንደኛው ሄዶ ዶሮዋን አርዶ መጣ፡፡ ሁለተኛው ግን ቆይቶ ዶሮዋን ሳያርዳት ይዟት ተመለሰ፡፡ “ምነው አላረድካት” ቢሉት “እርስዎ የሌሉበት ቦታ አጣሁ” አላቸው፡፡ (ሌላውን ለአንባቢ እንተዋለን፡፡)
አንድ ነክናካ (ነፍናፋ) ሼህ ፎቅ ቤታቸው ውስጥ ይኖሩ ነበር፡፡ ደርጉ መጣና የቤታቸውን ፎቁን ተወረሱና የቀበሌ ባለሥልጣን ገባበት፡፡ ለሳቸው ምድር ቤቱን ተውላቸው፡፡
እሳቸውም ቤቴን አስመልሱልኝ፤ ልወረስ አይገባኝም እያሉ ቀበሌ ጽህፈት ቤት እየተመላለሱ ሊቀ መንበሩን አሰለቹት፡፡ ማመልከቻ ይጻፉ ሲላቸው “እኔ ምኑን አውቄ እጽፈዋለሁ? አንተው ፃፍ ፃፍ አርግና እንደሚሆን አርገህ አስመልስልኝ፡፡
እሱም አላስመለሰላቸውም እሳቸውም መመላለሳቸውንም አልተው፡፡ በመጨረሻም “ወይም ፎቁን እርስዎ ይውሰዱትና ምድር ቤቱን ለሱ ይስጡት” አላቸው፡፡ “እንዲያ ካላችሁኝ መልካም!” ብለውት ሄዱ፡፡
በነጋታው ጧት ፎቃቸው ውስጥ ይኖር የነበረው ባለሥልጣን ሞቶ ተገኘ፡፡ ሊቀ መንበሩ መጥቶ “ምን ተደረገ እነ ሼህ?” ቢላቸው “ምድር ቤቱን ስጠው አላችሁኝ፤ ምድር ቤቱን ሰጠሁት” አሉት፡፡
- ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ‹‹አንድ ሺ ከአንድ ሌሊቶች›› (1987)