ትንጎራደዳለች ውበት ተጎናጽፋ
እንደ ሌላ አገሮች ሌቱ ደመና አልባ
ጨለማውም ይሁን ብርሃኑም የላቀ ከዋክብት የሞላ፤
የተወሃሃዱት ዓይኗን ገጽታዋ
እንደዚህ ስትፈካ በለስላሳው ብርሃን
እግዜር የነፈገው ለጠራራው ቀን።
ቅንጣት ጥላም ትሁን፤ ብታንስ አንዲት ጮራ፤
ግማሽ ያጎድለዋል ያን ስም የለሽ ፀጋ
የተጎነጎነው በጥቁር ጎፈሬ ሹርባዋ ዞማ፤
ወይ ለስላሳው ብርሃን ፊቷ ላይ ያበራ –
የመሠከሩበት ሃሳቦች የጣሙ በጥሞና እርጋታ
ውብም ነው ተወዳጅ ያረፉበት ቦታ።
በዚያች ጉንጭና ቅንድብ ሽፋሽፍት፤
ለስላሳም፤ የረጋ፤ ሆኖም የተሟላ ርቱዕ አንደበት፤
ፈገግታዋ ኃያል፤ ቀለሟ የጋለ፤
ደግሞም የሚያሳብቅ በምሥራች ቀናት በደስታ የዋለ፤
ሰላማዊው መንፈስ፤ ከዚያም በታች ያልፋል፤
የልቧ ፍቅርም በቅንነት ሞልቷል።
- ከጆርጅ ጎርደን ባይረን/ነፃ ትርጉም በዳዊት ዘኪሮስ