Sunday, September 24, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[በተቋሙ ሠራተኞች የተወከሉ አንድ ባልደረባ ሚኒስትሩን ለማነጋገር ቀጠሮ ይዘው ወደ ቢሯቸው ገቡ]

  • ጤና ይስጥልኝ ክቡር ሚኒስትር?
  • ሰላም ሰላም … ተቀመጥ!
  • አመሠግናለሁ ክቡር ሚኒስትር! ቀድሜ ቀጠሮ እንዲያዝልኝ ስጠይቅ እንደገለጽኩት በተቋሙ ሠራተኛ ተወክዬ ነው የመጣሁት።
  • እንዴ? አንተ የእኛ ተቋም ባልደረባ አይደለህም እንዴ?
  • ነኝ ክቡር ሚኒስትር!
  • ታዲያ በየትኛውን ተቋም ሠራተኛ ነው የተወከልከው?
  • በዚሁ በእኛው ተቋም ሠራተኛ ነው የተወከልኩት ክቡር ሚኒስትር።
  • እንዴት? በቀጥታ ከሠራተኛው ጋር የምገናኝበት መድረክ እያለ አንተን መወከል ለምን አስፈለገ?
  • የሠራተኛውን የኑሮ ሁኔታ የሚመለከት ስለሆነ በዕድሜም በልምድም አንተ ብታነጋግራቸው ይሻላል ብለው ስለወከሉኝ ነው።
  • ምንድነው ጉዳዩ?
  • ክቡር ሚኒስትር ሠራተኛው በኑሮ ውድነት እየተሰቃየ ነው።
  • እሱ የሁላችንም ችግር ነው … በአገር ጭምር የመጣ ነው።
  • ክቡር ሚኒስትር የመንግሥት ሠራተኛው ግን የከፋ ችግር ውስጥ ነው ያለው። በተለይ ተቋማችን …
  • ለተቋማችን ተለይቶ የመጣ ችግር ነው እንዴ?
  • አይለደም። ግን የችግሩን ጥልቀት የሚረዳልን አጥተናል።
  • ምን ማለትህ ነው?
  • ክቡር ሚኒስትር እኛ ተቋም ውስጥ ያለውን ሁኔታ ቢያዩ የችግሩን ጥልቀት ይረዱታል። በቀን አንዴ ብቻ የሚመገቡ ባልደረቦቻችን እየተበራከቱ ነው።
  • እና ምን ይደረግ ነው የምትለው? ለዚህ ተቋም ብቻ የሚወሰን ነገር እንደማይኖር አታውቅም?
  • እሱን እገነዘባለሁ። በሠራተኛው የተወከልኩትም እርስዎ መፍትሔ እንዲሰጡን አይደለም።
  • እና ለምንድነው?
  • ከፍተኛ የመንግሥት አመራር እንደመሆንዎ መጠን የሚመሩት ተቋም ሠራተኞችን ችግር ለካቢኔ እንዲያቀርቡልን ወይም ጉዳዩ ሲነሳ እንዲያስረዱልን ነው።
  • ጉዳዩ እንዴት ይነሳል? ማን ያነሳዋል?
  • በሁሉም የመንግሥት ተቋማት ያሉ ሠራተኞች ተመሳሳይ ጥያቄ ይኖራቸዋል ወይም የዚህ ተቋም ሠራተኞች እኔን እንደወከሉት ሌሎቹም እንደዚያ ሊያደርጉ ይችላሉ ብዬ ነው።
  • እሺ ተነሳ እንበል …
  • ከተነሳማ በዚህ ተቋም ያሉ ሠራተኞች ያሉበትን አስከፊ ሁኔታ እንዲያስረዱልንና መፍትሔ እንዲጠይቁልን ነው፡፡
  • ምን ብዬ ነው መፍትሔ የምጠይቀው?
  • ሠራተኛው በሚያገኘው ደመወዝ የኑሮ ውድነቱን ለመቋቋም አልቻለም ይበሉልን።
  • እሺ … ከዚያስ?
  • ከዚያማ ሠራተኛው የደመወዝ ጭማሪ ጥያቄ እያቀረበ ነው ሊጨመርለት ይገባል ይበሉልን!
  • እሺ እንደዚያ አልኩ እንበል። ለደመወዝ ጭማሪ የሚሆነው በጀት ከየት እንደሚመጣ አመላክት ብባልስ?
  • እሱን በጋራ የምትመልሱት እንጂ ለእርሶ ብቻ የሚተው አይመስለኝም።
  • በጋራ መፍትሔ ለመስጠትም እኮ ሐሳብ ማቅረብ ይጠይቃል።
  • ክቡር ሚኒስትር መንግሥት የሠራተኛውን ችግር በቅንነት ከተመለከተውና ካሰበበት መፍትሔ አይጠፋም።
  • አይ አንተ … እስኪ መፍትሔ ጠቁም ብትባል አንድ መፍትሔ የለህም ለማማረር ግን…
  • ክቡር ሚኒስትር በእርሶ ያምራል ብዬ እንጂ ጠቁም ካሉኝማ እጠቁማለሁ!
  • እስኪ በላ … ?
  • መቼም የጫካ ቤተ መንግሥት ፕሮጀክት ይታጠፍ አልልም።
  • እ … ብትልስ?
  • እኔም አልልም ግን …
  • ግን ምን ልትል?
  • ይዘግይና ሰው እንታደግ እላለሁ!
  • አሃ … ለዚህ ነው የመጣኸው?
  • ክቡር ሚኒስትር በቀን አንዴ ብቻ ተመግበው የሚውሉ ባልደረቦቻችን ቁጥር እየጨመረ ነው። ጥያቄያችን ከፖለቲካ ንፁህ መሆኑንም እንዲረዱኝ እፈልጋለሁ።
  • እንዴት ነው ከፖለቲካ ንፁህ የሚሆነው?
  • እውነቴን ነው ክቡር ሚ;ለስትር!
  • እውነቱ ምንድነው?
  • የኑሮ እንጂ የፖለቲካ ጥያቄ የለንም ክቡር ሚኒስትር!
  • የቤተ መንግሥት ግንባታ ይቁም እያልክ?
  • መፍትሔ ጠቁም ስላሉኝ ነዋ!
  • ብልህስ? የቤተ መንግሥት ግንባታ ይቁም ትላለህ?
  • ተከራከር ካሉኝም ሠራተኛው እየተራበ ቤተ መንግሥት መገንባት ቅደም ተከተሉን የጠበቀ መስሎ አይታየኝም።
  • ይኸው … ዋናው ጉዳይህ ቤተ መንግሥቱ ነው።
  • አይደለም ክቡር ሚኒስትር!
  • እየሰማሁህ?
  • ክቡር ሚኒስትር ጉዳዬ መንግሥት ችግሩን ተረድቶ ደመወዝ እንዲጨምር መጠየቃችንን እንዲያስረዱልን ነው። ካልሆነ ደግሞ …
  • ካልሆነ ምን?
  • ደመወዝ ካልሆነ ደግሞ ለተማሪዎች እንደተዘጋጀው ለእኛም እንዲዘጋጅልን ነው።
  • ለእኛም ማለት?
  • ለመንግሥት ሠራተኛው ማለቴ ነው?
  • ለመንግሥት ሠራተኛው ምን ይዘጋጅ ነው ምትለው?

–        የምገባ ፕሮግራም!

–         

 

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

በቀይ ባህር ፖለቲካ ላይ በመከረው የመጀመሪያ ጉባዔ ለዲፕሎማቲክና ለትብብር አማራጮች ትኩረት እንዲሰጥ ጥሪ ቀረበ

ሰሞኑን በአዲስ አበባ ለመጀመርያ ጊዜ በቀይ ባህር ቀጣና የፀጥታ...

የቤት ባለንብረቶች የሚከፍሉትን ዓመታዊ የንብረት ታክስ የሚተምን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በአዋጁ መሥፈርት መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የንብረት ታክስ መጠን...

እንደ ንብረት ታክስ ያሉ ወጪን የሚያስከትሉ አዋጆች ከማኅበረሰብ ጋር ምክክርን ይሻሉ!

የመንግሥትን ገቢ በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የሚታመኑት የተጨማሪ እሴት...

ለዓለምም ለኢትዮጵያም ሰላም እንታገል

በበቀለ ሹሜ ያለፉት ሁለት የዓለም ጦርነቶች በአያሌው የኃያል ነን ባይ...

የመጀመርያ ምዕራፉ የተጠናቀቀው አዲስ አበባ ስታዲየም የሳር ተከላው እንደገና ሊከናወን መሆኑ ተሰማ

እስካሁን የሳር ተከላውን ጨምሮ 43 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጓል ዕድሳቱ...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ለሁለት ቀናት የተካሄደውን የፓርቲያቸውን የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ አጠናቀው ወደ ቢሯቸው ሲመለሱ ቢሯቸው ውስጥ አማካሪያቸው አንድ ጽሑፍ በተመስጦ እያነበበ አገኙት]

ምንድነው እንደዚህ መስጦ የያዘህ ጉዳይ? መጡ እንዴ ክቡር ሚኒስትር፣ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ያወጣውን መግለጫ እያነበብኩ ነው፡፡ ግን እኮ ፊትህ ላይ የመገረም ስሜት ይነበባል፡፡ አዎ፣ መግለጫው ላይ...

[ክቡር ሚኒስትሩ እየጠራ ያለውን ሞባይል ስልካቸውን ተመለከቱ፣ የህዳሴ ግድቡ ተደራዳሪ መሆናቸውን ሲያውቁ ስልኩን አነሱት]

ሃሎ... ጤና ይስልጥኝ ክቡር ሚኒስትር? ጤና ይስልጥልኝ ክቡር ተደራዳሪ... የጥረትዎን ፍሬ በማየትዎ እንኳን ደስ አለዎት፡፡ እንኳን አብሮ ደስ አለን፣ ምን ልታዘዝ ታዲያ? የውኃ ሙሌቱንና አጠቃላይ የግድቡን የግንባታ ሁኔታ...

[የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሩ ክቡር ሚኒስትር ሌሊቱን በእንቅልፍ ልባቸው በህልም እየተወራጩ ሳለ የሞባይል ስልካቸው ጥሪ አነቃቸው። አለቃቸው ስለነበሩ ስልኩን በፍጥነት አነሱት]

በሌሊት ስለደወልኩኝ ይቅርታ፡፡ ችግር የለውም ክቡር ሚኒስትር፣ ምን ልታዘዝ? አንድ የአውሮፓ ባለሥልጣን ነገ በጠዋት ወደ አዲስ አበባ ይገባል። እሺ። ሌሎች የመንግሥት አመራሮች ስላልቻሉ እርስዎ መንግሥትን ወክለው ቦሌ ኤርፖርት...