Wednesday, November 29, 2023
Homeስፖንሰር የተደረጉከብሔራዊ ባንክ እውቅና ያገኘው ፔይሊንክ አክሲዮን ማህበር ምሥረታውን አካሄደ

ከብሔራዊ ባንክ እውቅና ያገኘው ፔይሊንክ አክሲዮን ማህበር ምሥረታውን አካሄደ

Published on

- Advertisment -

ከገንዘብ ንክኪ ነፃ የሆነ የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ለመተግበር ያቀደው የፔይሊንክ ፔይመንት ፕሮሰሲንግ አክሲዮን ማህበር ከብሔራዊ ባንክ በፔይመንት ጌት ዌይ ኦፕሬተርነት እውቅና አግኝቶ ምሥረታውን አካሄደ።

ፔይሊንክ ፔይመንት ፕሮሰሲንግ የከፍያ ስርዓት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ሞያዊ ድጋፍና ማበረታቻ ተደርጎለትና የኩባንያውን ምስረታ እንዲያካሂድ ከባንኩ እውቅና አግኝቶ የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤውን ህዳር 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በማካሄድ የኩባንያውን ምሥረታ መፈጸሙን የአክኪዮን ማሕበሩ ዋና አደራጅ አቶ ዳዊት ኪሮስ በላይ ገልጸዋል።

 

ፔይሊንክ ፔይመንት ፕሮሰሲንግ አክሲዮን ማህበር በ10 መስራች አባላት የተቋቋመ ሲሆን ፣ እያንዳንዳቸው 1000 ብር መጠን ያላቸው 3000 አክሲዮኖችን በመሸጥ በ ሦስት ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል እንደተመሠረተም ገልጸዋል።

ከብሔራዊ ባንክ እውቅና ያገኘው ፔይሊንክ አክሲዮን ማህበር ምሥረታውን አካሄደ | Ethiopian Reporter | ሪፖርተርፔይሊንክ ኩባንያ የዲጂታል የክፍያ ስርዓትን በማበልጸግ ከባንኮችና ከተለያዩ የንግድ ተቋማት ጋር በመተሳሰር ከገንዘብ ንክኪ ነፃ የሆነ ዘመናዊ የክፍያ ስርዓትን ለመፍጠር አልሞ እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም ዋና አደራጁ ገልጸዋል።

“በቀጣይ የኩባንያውን ተሞክሮ የበለጠ በማጎልበት ፣ ከውጪ ሃገር እና ከሃገር በቀል የዘርፉ አንቀሳቃሶች ጋር በመሥራት፣ አሁን በሀገራችን ያለውን የክፍያና የግብይት ሥርዓት በማዘመን የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ዕቅድን ለማሳካት የራሳችንን አስተዋጽኦ ለማኖር በሙሉ ዝግጅት ላይ እንገኛለን” ሲሉ ዋና አደራጁ ገልጸዋል።

የቅርብ ጊዜ መጣጥፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸማቸውን ለተከበረው ምክር ቤት ካቀረቡ በኋላ ከምክር ቤቱ አባላት የሚነሱ ጥያቄዎችን እየተቀበሉ ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው]

ክቡር ሚኒስትር መንግሥት ለሕዝብ ይፋ ያደረገው ነገር ከምን እንደደረሰ ቢያብራሩልን? ምንድነው ይፋ ያደረገው? ጥያቄውን ትንሽ...

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ ነዋሪዋ ወጣት፣ ባለፈው ሳምንት ለሦስት...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች ውስጥ ሲሚንቶ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው፡፡...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ እምለው” ዓምድ ላይ፣ “ብሔር ተኮር...

ተመሳሳይ

ለሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ አባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ጥሪ

ለሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ አባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ጥሪ ሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ መደበኛ እና ድንገተኛ ጠቅላላ...

ሴት ተማሪዎችን የማብቃት ትልም አንግቦ እየሠራ የሚገኘው ዲሳቱ አይስ ፋውንዴሽን

በየዓመቱ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡም ሆነ ከገቡ በኋላ በጥሩ ውጤት ተመርቀው ለቁም ነገር የሚበቁ ሴት ተማሪዎች...

Unlocking Sustainable Change: The Dalberg Approach to Impact-driven Innovation

Dalberg Advisors, a global impact consultancy committed to building a more inclusive and sustainable...