Thursday, June 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በሴካፋ ውድድር ታንዛንያን ይገጥማል

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በሴካፋ ውድድር ታንዛንያን ይገጥማል

ቀን:

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በምሥራቅና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ እግር ኳስ ውድድር (ሴካፋ) የዞን ማጣሪያ ውድድር ታንዛንያን ይገጥማል፡፡ ከሳምንታት በፊት ጀምሮ ሲዘጋጅ የነበረው ብሔራዊ ቡድኑ፣ ሱዳን በምታዘጋጀው  ውድድር ላይ ለመካፈል ከቀናት በፊት ወደ ሥፍራው ያቀና ሲሆን፣ ዛሬ ረቡዕ ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም. ታንዛንያን ይገጥማል፡፡

በአሠልጣኝ ዕድሉ ደረጀ የሚመራው ብሔራዊ ቡድኑ፣ ሰኞ ጥቅምት 21 ቀን የመጀመሪያ ልምምዱ ያደረገ ሲሆን፣ በምድብ ሁለት ከዑጋንዳና ከታንዛንያ ጋር ተደልድሏል፡፡ በምድብ አንድ ብሩንዲ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳንና ጂቡቲ ተደልድለዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጋር የተደለደሉት ዑጋንዳና ታንዛንያ ባደረጉት የምድቡ የመጀመሪያ ጨዋታ ዑጋንዳ 2 ለ 0 ማሸነፍ ችሏል፡፡

ከ20 ዓመት በታች የሴካፋ ውድድር ለ14ኛ ጊዜ የሚከናወነው ከጥቅምት 18 ቀን እስከ ኅዳር 2 ቀን ድረስ ነው፡፡ ውድድሩን በበላይነት ከየምድባቸው አንደኛና ሁለተኛ ሆነው የሚያጠናቅቁ አገሮች እ.ኤ.አ. በ2023 በግብፅ ለሚከናወነው ከ20 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ይሳተፋሉ፡፡

ኢትዮጵያ የምድቧን ሁለተኛ ጨዋታ እሑድ ጥቅምት 27 ቀን ከዑጋንዳ ጋር ታደርጋለች፡፡ አሠልጣኝ ዕድሉ ደረጀን በአሠልጣኝነት ይፋ ያደረገው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን 43 ተጫዋቾችን መርጦ ለሳምንታት ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡

ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2020 የሴካፋ ውድድር ከኬንያና ከሱዳን ጋር ተደልድላ የነበረ ሲሆን፣ ሱዳንን 3 ለ 2 ብትረታም በኬንያ 3 ለ 0 በመሸነፏ ከምድቧ ማለፍ አልቻለችም ነበር፡፡ 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...