Wednesday, December 6, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበመንግስትና ሕወሃት መካከል የሚደረገው የሰላም ውይይት ለመጪው ሰኞ ተጠራ

በመንግስትና ሕወሃት መካከል የሚደረገው የሰላም ውይይት ለመጪው ሰኞ ተጠራ

ቀን:

በአፍሪካ ኅብረት አመቻችነት የሚደረገው የመንግስትና የሕወሃት የሰላም ንግግር ለመጭው ሰኞ ጥቅምት 14 ቀን 2015 ዓ.ም መጠራቱን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደህንነት አማካሪ ሚንስትር ሬድዋን ሁሴን (አምባሳደር) በይፋዊ ማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስታውቀዋል፡፡
 
በቀረበው የሰላም ውይይት ላይ መንግስት ለመሳተፍ ቁርጠኛ መሆኑን ያረጋገጡት ሚንስትሩ፣ ሆኖም አንዳንዶች መንግስት በሚወስደው “ራስን የመከላከል እርምጃ” ላይ ሃሰተኛ ውንጀላዎችን በማሰራጨት የተጀመረውን የሰላም ውይይት ለማደናቀፍ እየጣሩ መሆኑን በመግለፅ ወቅሰዋል፡፡
የሰላም ንግግሩ ለመጪው ሰኞ የተቀጠረው ከዚህ ቀደም የአፍሪካ ህብረት ከሁለት ሳምንት በፊት ንግግሩን ለማስጀመር ያስተላለፈው ቀጠሮ ከተሰረዘ በኋላ ነው፡፡
 
ህብረቱ የመጀመሪያውን ጥሪ አስመልክቶ በላከው ደብዳቤ፣ ንግግሩ የሚመቻቸው በአፍሪካ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ተወካይ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆና ሌሎች ስመጥር አፍሪካውያን መሆኑን አስታውቆ ነበር፡፡
 
ከኦሉሴጉን ኦባሳንጆ በተጨማሪ ንግግሩን እንደሚያመቻቹ የተገለፁት የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታና የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዝዳንትና በአሁኑ ወቅት የሕብረቱ የሰላምና ደህንነት ምክር ቤት አማካሪ (ፓነል ኦፍ ዘ ዋይዝ) አባል የሆኑት ፉምዙሌ መላምቦ ንጉካ ናቸው፡፡
spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...