Wednesday, December 6, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ መንግሥት ሰሞኑን ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ላይ የጣለውን ክልከላ ማኅበረሰቡ እንዴት እንደተቀበለው ከአማካሪያቸው ጋር እያወሩ ነው]

  • እሺ ተቃውሞ ሰማሁ ነው ያልከኝ?
  • አዎ ክቡር ሚኒስትር። እንዳይገቡ ከተከለከሉት ምርቶች በተወሰኑት ላይ ተቃውሞ ሰምቻለሁ።
  • በየትኞቹ ምርቶች ላይ?
  • በተለይ አርቴፊሻል ፀጉር በመከልከሉ በርካታ ተቃውሞና ትችት በማኅበራዊ ድረገጾች ሲዘዋወር ነበር። 
  • የኡጋንዳዋ ምክትል ፕሬዚዳንት የተናገሩትን ሰምተው ቢሆን ይቃወሙም ነበር።
  • የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዚዳንት? 
  • አዎ። ሰሞኑን በባህርዳር በተካሄደው የጣና ፎረም ላይ ንግግር አድርገው ነበር። 
  • አዎ። እርስዎም እዚያ ነበሩ። እና ሴትየዋ ምን አሉ? 
  • የኡጋንዳ ወጣት ሴቶች በፀጉራቸው ማጠር ደስተኛ አለመሆናቸውን በቀልድ መልክ ይናገራሉ አሉ።
  • ምን ብለው ይናገራሉ አሉ?
  • ማነው ከአቢሲኒያ ያመጣን! ወደ ኡጋንዳ ባያመጡን ኖሮ እንደ ኢትዮጵያውያን ሴቶች ፀጉራችን ያምር ነበር እንደሚሉ ተናግረው ነበር።
  • [ሳቅ] የሚገርመው ግን አርቴፊሻል ፀጉር እንዳይገባ መከልከሉን የተቃወሙት ሴቶቻችን አይደሉም ክቡር ሚኒስትር።
  • እንዴ! እና ማነው የተቃወመው?
  • ሸኔ፡፡ 
  • [እየሳቁ] አንተ ደግሞ ቀልድና ቁምነገርህ አይለይም። 
  • ምን ላድርግ ብለው ነው ክቡር ሚኒስትር።
  • ልክ ነህ እንደዚህ ቁምነገር ያዘሉ ቀልዶች ያዝናናሉ። 
  • ልክ ነው ክቡር ሚኒስትር። 
  • ሌላ የሰማኸው ተቃውሞ ነገር የለም? 
  • ልሂቃኑን ጨምሮ አብዛኛው የማኅበረሰብ ክፍል ውሳኔያችንን በከፍተኛ ደረጃ ነው የደገፈው። ግን ደግሞ…
  • ግን ምን?
  • ያው ተቃውሞ ጨርሶ አይጠፋም። በተለይ ተቃውሞው ከራሳችን መዋቅር መመንጨቱ በጣም ያበሳጫ።
  • ከራሳችን ስትል? ከሕዝብ ክንፍ ነው?
  • አይደለም። በየደረጃው ከሚገኙ የፓርቲና የመንግሥት መዋቅሮቻችን ማለቴ ነው።
  • አትለኝም? 
  • እውነቴን ነው ክቡር ሚኒስትር። 
  • እንዴት?
  • በተለይ ውስኪ እንዳይገባ መከልከል የለበትም የሚሉት መብዛታቸው አስገራሚ ነው። 
  • ይህ አስገራሚ አይደለም!
  • እ…
  • አሳፋሪ ነው!
  • አዎ፣ ያበሳጫል ክቡር ሚኒስትር።
  • ግን ውስኪ እንዳይገባ በመከልከሉ ብቻ ሲሉ ነው የተቃወሙት? 
  • ውስኪ ይበሉ እንጂ ምክንያታቸው እሱ እንዳልሆነ ይታወቃል።
  • ምንድነው ምክንያታቸው?
  • ጊዜ ነው 
  • የምን ጊዜ?
  • በእኛ ጊዜ እንዴት ይከለከላል ነው የሚሉት ክቡር ሚኒስትር
  • እነዚህን ነው በጊዜ ማለት!
  • በጊዜ ማለት ሲሉ?
  • በጊዜ መሸኘት!

[የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ መንግሥት የሰሜኑ ጦርነትን በተመለከተ መረጃ መስጠት ከጀመረ እኔም አንዳንድ ጉዳዮችን ልረዳ ብሎ በጠዋት ክቡር ሚኒስትሩ ቢሮ ገብቶ እየጠየቀ ነው]

  • እንደምን አደሩ ክቡር ሚኒስትር?
  • ሰላም። 
  • እንኳን ደስ አልዎት። 
  • ለምኑ?
  • የሰሜኑ ጉዳይ ወደ መደምደሚያው እየተጠጋ ይመስላል።
  • በዚህ ጉዳይ ላይ አትጠይቀኝ አላልኩህም?
  • መንግሥት ዝምታውን ሰብሯል ብዬ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • መንግሥት የተናገረው ነገር አለ እንዴ? 
  • አዎ። ትላንት መግለጫ አውጥቶ ሦስት ከተሞችን መቆጣጠሩን ይፋ አድርጓል። ከዚያ በፊትም የአየር ማረፊያዎችን እንደሚቆጣጠር ገልጿል። 
  • ለነገሩ ከዚህ በኋላ ዝም ማለት ጠቀሜታ የለውም። 
  • አዎ፣ ትክክል ነው። የውጭ አጋሮቻቸው ዝምታውን ተጠቅመው ጫና ለመፍጠር እየሞከሩ ነው። 
  • እኮ። እዚህ ደረጃ ሲደርስ መናገር ተገቢ ነው። ለዚያም ነው መንግሥት የተናገረው። 
  • ቢሆንም ያልገባኝ ነገር አለ ክቡር ሚኒስትር?
  • ምንድነው?
  • መንግሥት በይፋ አየር ማረፊያዎችን እቆጣጠራለሁ ማለቱ ትክልል ነው? የውጭ አጋሮቻቸውን አያስቆጣም?
  • ለምን ያስቆጣል? አየር ማረፊያዎቹ እኮ የፌዴራል መንግሥት ንብረቶች ናቸው። 
  • እሱስ ልክ ነው። 
  • በተጨማሪም የውጭ ኃይሎች አየር ማረፊያዎቹን ሊጠቀሙ እንደሚችሉ በምዕራባዊያኑ ጭምር የተረጋገጠ ተጨባጭ ማስረጃ በመኖሩ ነው። 
  • በራሳቸው የተረጋገጠ መረጃ አለ? 
  • አዎ። ራሳቸው ያረጋገጡትና በይፋም የተናገሩት ነው።
  • እንደው ግን ክቡር ሚኒስትር መንግሥት ከአየር ማረፊያዎቹ ውጪ ወደ ዋና ከተማዋ አይገባም?
  • በዋና ከተማ አየር ማረፊያ የለም እንዴ? 
  • አለ? 
  • ስለዚህ ይገባል። በዚያ ላይ አየር ማረፊያዎችን ብቻ አይደለም መንግሥት ለመቆጣጠር የወሰነው።
  • ሌላ ምን አለ?
  • የፌዴራል መንግሥት መሠረተ ልማቶችንም ይቆጣጠራል።
  • የትኞቹን ማለት ነው? 
  • ለምሳሌ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ የኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን፣ አገር አቋራጭ የትራንስፖርት መንገዶችን ይቆጣጠራል።
  • ዩኒቨርሲቲዎችም አሉ። 
  • እዎ። የመከላከያ ሠራዊቱ ይጠቀምባቸው የነበሩ የማዘዣ ማዕከላትንም ይቆጣጠራል። 
  • አሁን የገለጿቸው በሙሉ እኮ በዋና ከተማዋ ይገኛሉ።
  • ስለዚህ ይቆጣጠራቸዋል። 
  • እነዚህን ሁሉ ተቋማት ከሚቆጣጠር ሌላ ነገር ቢያደርግ አይሻለውም?
  • ምን?
  • ከተማዋን መቆጣጠር!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...

ኦሮሚያ ኢንሹራንስ በግሉ ኢንሹራንስ ዘርፍ ሁለተኛውን የገበያ ድርሻ ለመያዝ ያስቻለውን ውጤት ማስመዝገቡን ገለጸ

ኦሮሚያ ኢንሹራንስ ኩባንያ የባንኮች የጥሬ ገንዘብ እጥረት፣ የመለዋወጫ ዕቃዎች...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ ነው? እንዴት? አለቃዬ ዕረፍት የለው፣ እኔንም አላፈናፍን ብሎኛል። ታድለሽ። ታድለሽ? ሥራ ገደለኝ ዕረፍት አጣሁ እኮ ነው ያልኩሽ? ገብቶኛል። ምነው እኔንም...

[ክቡር ሚኒስትሩ የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸማቸውን ለተከበረው ምክር ቤት ካቀረቡ በኋላ ከምክር ቤቱ አባላት የሚነሱ ጥያቄዎችን እየተቀበሉ ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው]

ክቡር ሚኒስትር መንግሥት ለሕዝብ ይፋ ያደረገው ነገር ከምን እንደደረሰ ቢያብራሩልን? ምንድነው ይፋ ያደረገው? ጥያቄውን ትንሽ ቢያብራሩት? ከአራት ዓመት በፊት በኦጋዴን አካባቢ ነዳጅ መገኘቱን ለሕዝብ በቴሌቪዥን አብስሮ...

[ክቡር ሚኒስትሩ አንድ የካቢኔና የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ አባል የሆኑ ከፍተኛ አመራር የሚያቀርቡትን ቅሬታ እያደመጡ ነው] 

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር በእጅጉ ስላሳሰበኝ ነው በአካል አግኝቼ ላነጋግርዎት የፈለግኩት። ጥሩ አደረግህ፣ ምን አሳሳቢ ነገር ገጥሞህ ነው? ክቡር ሚኒስትር ተወያይተንና ተግባብተን ያስቀመጥናቸው አቅጣጫዎች፣ በተለይም...