Wednesday, June 7, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበቤንዚንና ነጭ ናፍጣ ላይ ጭማሪ ተደረገ

በቤንዚንና ነጭ ናፍጣ ላይ ጭማሪ ተደረገ

ቀን:

  • ከዛሬ መስከረም 18 ቀን 2015 ዓም እኩለ ሌሊት ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል

    የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ መደረጉንና ከዛሬ መስከረም 18 ቀን 2015 ዓም እኩለ ሌሊት ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ማምሻውን አስታወቀ፡፡

    ሚኒስቴሩ እንዳስታወቀው፣ በአዲስ አበባ ከተማ ቤንዚን በሊትር 57 ብር ከ05 ሳንቲም፣ ነጭ ናፍጣ በሊትር 59 ብር ከ90 ሳንቲም ፣ ኬሮሲን በሊትር 59 ብር ከ90 ሳንቲም ሆኗል፡፡

    ሌሎች የነዳጅ ውጤቶች ማለትም የአውሮፕላን ነዳጅ ፣ ቀላል ጥቁር ናፍጣና ከባድ ጥቁር ናፍጣ ባሉበት እንዲቀጥሉ መወሰኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

    በሌላ በኩል አነስተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በተዘረጋው የታለመ ድጎማ አሠራር ታቅፈው ሕዝቡን እንዲያገለግሉ የተመረጡት የሕዝብ ትራንስፖርት ተሽክርካሪዎች በሚጠቀሙት ነዳጅ ላይ በሁለተኛው ምዕራፍ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አለመደረጉንና ተሽከርካሪዎቹ በሐምሌ ወር በተወሰነላቸው ዋጋ መሠረት ቤንዚን በሊትር 41.26 ብር፣ ነጭ ናፍጣ በሊትር 40.86 ብር እየገዙ እንዲቀጥሉ ብቻ ሳይሆን፣ ከእጥፍ በላይ ያደገ ድጎማ ከመንግሥት እንዲያገኙ የተደረገ ስለሆነ በሚቀጥለው ጊዜ ዋጋ እስኪሻሻል ድረስ በሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ምንም ዓይነት ጭማሪ አለመደረጉን ንግድና ቀጠናዊ ትስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ንግድ ባንኮች በከፍተኛ የገንዘብ እጥረት ውስጥ መሆናቸው ተገለጸ

‹‹የገንዘብ እጥረት የሚገጥመው ያለውን ሀብት የማስተዳደር ችግር ስላለ ነው›› የኢትዮጵያ...

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ2,700 በላይ ሰዎች በትራፊክ አደጋ ሕይወታቸውን ማጣታቸው ተገለጸ

ከ1.7 ቢሊዮን ብር በላይ የንብረት ጉዳት ደርሷል በአበበ ፍቅር ባለፉት ዘጠኝ...

የአብዮታዊት ኢትዮጵያ የጦር ሜዳ ጀብዱ ኒሻን ተሸላሚው ሻለቃ ባሻ ዓሊ በርኬ (1943-2015)

ከአርባ ስድስት ዓመታት በፊት፣ ኢትዮጵያ ከወራሪው የሶማሊያ ሠራዊት ጋር...