Wednesday, November 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅትዳር ለመመሥረት

ትዳር ለመመሥረት

ቀን:

ስኮትላንዳዊው የጠገበ ሃብታም እንደ ዓይኑ ብሌን የሚንከባከባት አንዲት ሴት ልጅ ነበረችው፡፡ እንደብዙዎቹ ሃብታሞችም ልጁ የናጠጠ ነጋዴ እንድታገባ ይፈልግ ስለነበር ቤሳ ቤስቲኒ የሌለው የነጣ የገረጣ የሃይማኖት ተማሪ ልታገባ እንደሆነ ባሳወቀችው ጊዜ ጠንከር ያሉ ጥያቄዎችን አቀረበለት፡፡

“ገቢህ ምን ያክል ነው?”

”ምንም ብል ይሻላል፣ጌታዬ፡፡”

”ይህ በእግዚአብሔር እጅ ያለ ነገር ነው፤ ጌታዬ፡፡”

“ልጄን ታድያ በምን ታስተዳድራታለህ? “

“እግዜር ይሰጠኛል፡፡”

“ልጆች ብትወልዱስ ማን ያለብሳቸዋል፤ማንስ ይቀልባቸዋል? “

“ሁሉንም እግዜር ይሸፍነዋል ” አለ ወጣቱ በመተማመን፡፡

 ወጣቱ ወደ ቤቱ እንደሄደ የልጅቱ እናት ባለቤቷን “እንዴት አገኘኸው?” ስትል ጠየቀችው፡፡ “ሰውየው ገንዘብ ፤ሥራም ሆነ ተስፋ የለውም፡፡ በዚያ ላይ እኔ እግዚአብሔር ሳልመስለው አልቀረሁም፡፡”

  • አረፈዓይኔ ሐጐስ ‹‹የስኮትላንዳውያን ቀልዶች›› (2005)
spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...