Wednesday, November 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅዛፎች

ዛፎች

ቀን:

ከተፈጥሮ ጋር ስለአለው ግንኙነት አቶ ኮይነር ተጠይቆ፣ እንዲህ ሲል መልስ ሰጥቷል፡፡ «ከቤት ስወጣ አንድ ሁለት ዛፎችን ባይ ደስ ይለኛል፡፡ በተለይም በየቀኑ እና በየዓመቱ በተለያዩ ጊዜዎች በሚያገኙት የመልክ ለውጥ  የተነሣ የእውነትን ልዩ ደረጃ የሚጐናጸፉ ስለሆነ፡፡ ከዚህም ሌላ፣ በየከተሞቻችን ሁል ጊዜ የሚታዩት አገልግሎት ተቋሞች፣ ማለትም ቤቶች እና መንገዶች ብቻ ሲሆኑ፣ እነዚህም ካልተኖረባቸው ባዶ፣ ጥቅም ላይ ካልዋሉ ከንቱ ስለሚሆኑ፣ ቀስ በቀስ፣ እንወናበዳለን፡፡ የያዝነው ልዩ የኅብረተሰብ ሥርዓት፣ በበኩሉ፣ ሰዎችንም የእነዚህ የአገልግሎት ተቋሞች አካል አድርገን እንድንቆጥር፣ ተጽዕኖ አሳድሮብናል፡፡ ስለዚህም፣ ዛፎች ቢያንስ ቢያንስ ለእኔ፣ አናጢ ላልሆንኩት፣ እራሱን የቻለ የሚያረጋጋ እኔን በተለይ የማይመለከት አንድ የሆነ ነገር አላቸው፡፡ እንዲያውም እኔ ተስፋ የማደርገው፣ ዛፎች ለአናጢዎችም እንኳን ቢሆን ዋጋው በገንዘብ ብቻ የማይተመን ጥቅም ይኖራቸዋል ብዬ ነው፡፡»

      (ከዚህም ሌላ አቶ ኮይነር እንደዚህ አሉ፡፡) «ሰዎች በተፈጥሮ ስንጠቀም ፣አጠቃቀማችንን ቁጠባ አዘል ማድረግ ያስፈልገናል፡፡ ሥራ ፈትቶ በተፈጥሮ ውስጥ በመንቀዋለል ሰው በቀላሉ በሽታ ላይ ሊወድቅ ይችላል፣እንደ ትኩሳት ያለ ዱብዳ ላይ፡፡»

***

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...