Wednesday, November 29, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ አዲሱ ዓመት ሰላም ይዞ ይመጣል የሚል ተስፋቸውን ለባለቤታቸው እየገለጹ ነው]

  • መንግሥት አሁንም እጁን ለሰላም እንደዘረጋ ነው። ነገር ግን በዚያኛው ወገን ከጦርነት በቀር ሌላ ፍላጎት የለም።
  • ከዚህ አዙሪት በቀላሉ መውጣት ይቻላል ብለህ ታምናለህ?
  • አዲሱ ዓመት ሰላም ይዞ እንደሚመጣ ተስፋ አደርጋለሁ።
  • ዝም ብለህ ነው ተስፋ ያደረግከው።
  • እንዴት?
  • አዲስ ዓመት ከየት ያመጣዋል?
  • ተስፋ ማድረግ ጥሩ ነው! 
  • ለሰላም ዝግጅት ሳይኖር ተስፋ ማድረግ ሰላም ያመጣል?
  • በእኛ በኩል ዝግጁ ነን። እነሱ ግን እንደምታውቂው ናቸው።
  • በእናንተ በኩል ዝግጁ ስለመሆናችሁ እርግጠኛ ነህ?
  • በይፋ ደጋግመን እየገለጽን አይደል እንዴ? 
  • ታዲያ ምነው የሰላም ጥሪ ሊያቀርቡ የነበሩትን ከለከላችሁ? 
  • እነሱን ተያቸው… ሰላም ፈላጊዎች አይደሉም።
  • እና ምንድናቸው?
  • ተላላኪዎች! 
  • ኧረ …ተው?
  • ሰላም ፈላጊዎች ቢሆኑማ ሁሉም ሲጠቃ ድምጻቸውን እንሰማ ነበር። ተልከው እንደሆነ ብቻ ሳይሆን ማን እንደላካቸውም እናውቃለን።
  • ማን ይልካቸዋል?
  • በጀት የሚመድቡላቸው ልዩ መልዕክተኞች ናቸው።
  • ቢሆንስ ምን ችግር አለው?
  • የመልዕክተኞቹ ዓለማ ሰላም አይደለም። 
  • ታዲያ ምንድነው?
  • በሰላም ስም ፋታ ሊገዙለት ነው።
  • ለማን?
  • እየተቀጠቀጠ ላለለው አማጺ ወዳጃቸው ነዋ። 
  • ኧረ… ተው?
  • እንደዚያ ባይሆንማ ማጥቃት ከመጀመራችን በፊት በተደጋጋሚ ያቀረብነውን ሰላም ጥሪ ጆሮ ይሰጡት ነበር። ልክ ማጥቃት ስንጀምርና ስንገሰግስ ግን ስለ ሰላም መጮህ ጀመሩ።
  • እናተም ሆነ እነሱ የምትፈልጉት የሰላም ጥሪ አልመሰለኝም። 
  • ከሰላም ሌላ የምን ጥሪ እንፈልጋለን?
  • የክተት ጥሪ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአንድ የአውሮፓ አገር ዲፕሎማት ጋር ዳግመኛ ስለተቀሰቀሰው የሰሜኑ ጦርነትና ሰላም እንዴት ሊመጣ እንደሚችል እየተወያዩ ነው] 

  • ክቡር ሚኒስትር የሰሜኑ ጦርነት በሰላማዊ ድርድር ይፈታል ብለን ተስፋ ባደረግንበት ወቅት ዳግም ጦርነት መቀስቀሱ አሳዝኖናል።
  • እውነት ነው እኛም ችግሩን በሰላም ለመፍታት ተስፋ አድርገን ሳለ ወደ ጦርነት በመግባታችን በጣም አዝነናል። 
  • የአፍሪካ ኅብረትም ሆነ ሌሎች የአውሮፓ አደራዳሪዎች የጀመሩት የሰላም ጥረት ሊሳካ ጫፍ ላይ መድረሱን ነበር የሰማነው። 
  • ግን አልሆነም። ምክንያቱም ይህ ቡድን ያለ ጦርነት መኖር አይችልም። 
  • ስለዚህ ጦርነት ለመረዳት በጣም እየተቸገርን ነው ክቡር ሚኒስትር? 
  • እንዴት?
  • ያኛው ወገንም በተመሳሳይ መንግሥትን ይከሳል። እናንተም ያኛውን ወገን ትከሳላችሁ። በዚህ ሁኔታ ግራ ተጋብተናል። 
  • አምባሳደር ያኛው ወገን ግራ ማጋባት ልማዱ ነው። ከዚህ ወገን እውነትን መጠበቅ ነው። 
  • እነሱ መንግሥት ነው ጦርነቱን የጀመረው። ለሰላም ዝግጁ ነን ይላሉ። 
  • ችግሩ እናንተ ዘንድ ነው ያለው። 
  • እንዴት ክቡር ሚኒስትር?
  • ምክንያቱም እውነቱን ለማወቅ ሳይሆን ግራ ለመጋባት ነው የምትፈልጉት።
  • አልገባኝም ክቡር ሚኒስትር?
  • መንግሥት ጦርነቱን የሚጀምርበት ምክንያት የለም። ጦርነቱን በመጀመር የሚጠቀመው ነገር የለም። 
  • ግን እነሱም ጦርነቱን አልጀመርንም ይላሉ። 
  • የእነሱ ጦር በአንድ ቀን ወስጥ የቆቦ ከተማ ተቆጣጥሩ በቀጣዩ ቀን ደግሞ ወልዲያ ከተማ ዙሪያ እንዴት ሊደርስ ቻለ የሚለውን ጥያቄ መመለስ ከቻልክ ጦርነቱን ማን እንደጀመረ መረዳት ትችላለህ። 
  • እንዴት? 
  • በዚያ አቅጣጫ ጦርነት ለመክፈት ዝግጅት ካላደረክ ጦርህን ካላሰለፍክ በዚያ ፍጥነት ወልዲያ ዙሪያ ለመድረስ ፈጽሞ የሚቻል አይደለም። 
  • እህ…
  • ይህንን ለመቀበል የምትቸገሩ ከሆነ ደግሞ በቀላሉ መረዳት የምትችሉበትን ሌላ መንገድ መጠቆም ይቻላል።
  • እባክዎ ይንገሩኝ ክቡር ሚኒስትር?
  • በዚሁ ግንባር የማረኩትን አንድ የእኛ ጦር ሠራዊት አባልን በራሳቸው ሚዲያ ቃለመጠይቅ አድርገውለት የነገራቸውን ፈልገህ አድምጥ።
  • እባክዎ ምን አንዳላቸው በአጭሩ ይንገሩኝ? 
  • የአሁኑ ጦርነት የጀመረው እርሱ በነበረበት የቆቦ ግንባር እንደሆነና የእነሱ ጦር ከጀርባ ቆርጦ በመግባት በአራት አቅጣጫ እንዳጠቃቸው ነግሯቸዋል።
  • እሺ…?
  • የእነሱ ጦር በጀርባ ቆርጦ መግባቱን ለበላይ አመራር አሳውቆ ድጋፍ ሰጪ ኃይል እንደሚላክለት ተነግሮት ምሽግ ውስጥ እንደቆየ ሁሉ ያስረዳል። 
  • እሺ…
  • ነገር ግን ሁኔታው ፈጣን እንደነበርና ከበባውን ሰብሮ መውጣት እንዳልቻለ በዚህም ምክንያት ቆስሎ መያዙን ገልጾላቸዋል። ግን…
  • ይቀጥሉ ክቡር ሚኒስትር…
  • ይህንን ቃለ ምልልስ በይፋ አስተላልፈውም ጦርነቱን የጀመረው መንግሥት ነው እያሉ ማደናገራቸው የሚጠበቅ ነው።
  • ክቡር ሚኒስትር አሁንም ለሰላም አልረፈደም።
  • እኛም ሰላም ነው የምንፈልገው አምባሳደር። ጦርነት ተከተፍቶብንም ቢሆን ሰላም ነው የምንሻው። 
  • እነሱም ሰላም እንደሚፈልጉ ገልጸውልናል።
  • እናንተስ አምባሳደር? 

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...

ሀብቱንና ትርፉን እያሳደገ የቀጠለው አዋሽ ባንክ

አዋሽ ባንክ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ዋና መሥሪያ ቤት...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸማቸውን ለተከበረው ምክር ቤት ካቀረቡ በኋላ ከምክር ቤቱ አባላት የሚነሱ ጥያቄዎችን እየተቀበሉ ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው]

ክቡር ሚኒስትር መንግሥት ለሕዝብ ይፋ ያደረገው ነገር ከምን እንደደረሰ ቢያብራሩልን? ምንድነው ይፋ ያደረገው? ጥያቄውን ትንሽ ቢያብራሩት? ከአራት ዓመት በፊት በኦጋዴን አካባቢ ነዳጅ መገኘቱን ለሕዝብ በቴሌቪዥን አብስሮ...

[ክቡር ሚኒስትሩ አንድ የካቢኔና የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ አባል የሆኑ ከፍተኛ አመራር የሚያቀርቡትን ቅሬታ እያደመጡ ነው] 

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር በእጅጉ ስላሳሰበኝ ነው በአካል አግኝቼ ላነጋግርዎት የፈለግኩት። ጥሩ አደረግህ፣ ምን አሳሳቢ ነገር ገጥሞህ ነው? ክቡር ሚኒስትር ተወያይተንና ተግባብተን ያስቀመጥናቸው አቅጣጫዎች፣ በተለይም...

[ጉባዔው በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ክቡር ሚኒስትሩን ለመጠየቅና ምላሽና ማብራሪያቸውን ለማድመጥ ተሰብስቧል። የጉባዔው አባላትም ማብራሪያ የሚሹ ጥያቄዎቻቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር፣ ይህ ጉባዔ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ለመስጠት በመካከላችን ስለተገኙ አመሰግናለሁ። ክቡር ሚኒስትር፣ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት የብሪክስ አባል እንድትሆን የሰጡት በሳል አመራር የሚደነቅ ነው። አገራችን...