ውሻው ደንዲ ከተማ (ስኮትላንድ) የሚገኝ ሥጋ ቤት ዘሎ ገብቶ ሊቆረጥ ከተደረደረው ሥጋ በቅርቡ ያገኘውን መንትፎ ይሄዳል፡፡ ውሻው የጠበቃው ጐረቤቱ መሆኑን ያወቀው ባለ ሥጋ ቤት ስልክ ደውሎ “ውሻህ ከልኳንዳዬ ለጥብስ የሚሆን ምርጥ ሥጋ ቢሰርቅ ለደረሰብኝ ኪሳራ ተጠያቂ ትሆናለህ ወይ?” ሲል ይጠይቀዋል፡፡
“በሚገባ እንጂ፤ ለመሆኑ የሥጋው ዋጋ ስንት ነው?”
“ሰባት ፓውንድ ነው” አለ ባለሥጋ ቤቱ ተደስቶ፡፡
ከጥቂት ቀናት በኋላ ለባለ ሥጋ ቤቱ በፖስታ ቤት በኩል የሰባት ፓውንድ ቼክ ደረሰው፡፡ ከቼኩ ጋርም “ለምክር አገልግሎት የተጠየቀ ሒሳብ 150 ፓውንድ” የሚል ኢንቮይስ ተያይዞ ነበር፡፡