Tuesday, March 28, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅ‹‹ወደ ትምህርት ቤት›› ኤግዚቢሽንና ባዛር እስከምን?

‹‹ወደ ትምህርት ቤት›› ኤግዚቢሽንና ባዛር እስከምን?

ቀን:

ከነሐሴ 26 ቀን ጀምሮ የተማሪዎች የትምህርት ግብዓት በቅኛሽ ዋጋ የሚሸጥበት ኤግዚቢሽንና ባዛር በጊዮግ ሆቴል ቅጥር ግቢ እንደሚካሄድ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ማስታወቂያዎች ሲነገሩ ሰንብተዋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ ወላጆች ቅናሽ ዋጋ እናገኛለን ብለው ኤግዚቢሽኑ በተከፈተበት ዕለት በሥፍራው ተገኝተዋል፡፡ ሪፖርተር በቦታው ተገኝቶ እንደታዘበው፣ በሥፍራው በዕለቱ ከነበሩ 20 ያህል ድንኳኖች ከአምስት ያልዘለሉት ብቻ የተማሪዎች ቁሳቁስ የያዙ ሲሆን፣ ዋጋውም ከገበያ ዋጋ ይበልጥ እንደሆነ እንጂ የቀነሰ አልነበረም፡፡ የመግቢያ 100 ብር ከፍለው የገቡ ሸማቾች በሥፍራው በማስታወቂያ የተነገረውን ያህል ባለማግኘታቸው ሲያማርሩ እንደነበርም ታዝበናል፡፡ ኤግዚቢሽኑ በተከፈተበት ነሐሴ 26 ቀን 2014 ዓ.ም. ራዲካል ደብተር በደርዘን 900 ብር፣ ሲነርላይን በደርዘን 650 ብር እንዲሁም በአገር ውስጥ የተመረተ ደብተር 500 እና 600 መቶ ብር በደርዘን እየተሸጠ ነው፡፡ የተማሪ ቦርሳ ከ650 ብር (ለጀማሪ) እስከ 950 ብር እንደሚሸጡ፣ የተማሪ ምሳ ዕቃ ደግሞ ይህንንም ያህል እንዳልነበረ ለመታዘብ ችለናል፡፡ በሥፍራው የነበሩ ወላጆችም በሁኔታው ሲበሳጩ አይተናል፡፡‹‹ወደ ትምህርት ቤት›› ኤግዚቢሽንና ባዛር እስከምን? | Ethiopian Reporter | ሪፖርተር‹‹ወደ ትምህርት ቤት›› ኤግዚቢሽንና ባዛር እስከምን? | Ethiopian Reporter | ሪፖርተር

  • ፎቶ በመስፍን ሰሎሞን
spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

‹‹ከኦነግ ሸኔ ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት አለን›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ

መንግሥት ከ‹‹ኦነግ ሸኔ››ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት...

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...