Saturday, March 25, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ ከፖለቲካ አማካሪያቸው ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ እየተወያዩ ሳለ አማካሪያቸው ባነሳው አንድ ጥያቄ ተበሳጩ]

  • ክቡር ሚኒስትር፣ እንዲያው ይቅርታ ያድርጉልኝና አንድ ጥያቄ ልጠይቅዎት እችላለሁ?
  • ምን ዓይነት ጥያቄ ቢሆን ነው? ለማንኛውም ጠይቀኝ ችግር የለውም። 
  • በእርስዎ እምነት ገዥው ፓርቲ ከሠራቸው ስኬታማ ሥራዎች ግንባር ቀደም የሚሉት ምንድነው? 
  • ከባድ ጥያቄ ነው፡፡
  • እንዴት? 
  • ምክንያቱም ለማበላለጥ ይከብዳል፣ ከወለድካቸው ልጆችህ ወይም ከእጅህ ጣቶች መካከል የቱን አስበልጠህ ትወዳለህ እንደ ማለት ነው፣ ለእኔ ሁሉም ስኬቶች እኩል ናቸው ማለት ይቀለኛል።
  • አርቲስት ነው የመሰሉኝ ክቡር ሚኒስትር። 
  • እንዴት? 
  • እነሱ ናቸው ብዙ ጊዜ እንዲህ ዓይነት መልስ የሚሰጡት፣ በተለይ በሚዲያ በሚተላለፉ የበዓል ፕሮግራሞች ላይ።
  • ለመሆኑ ለምንድነው የጠየቅከኝ? ልትነግረኝ የፈለግከው ነገር አለ? 
  • እንደዚያ ሳይሆን ነገሩ ቢያስገርመኝ ነው እርስዎን መጠየቅ የፈለግኩት። 
  • ያስገረመህ ነገር ምንድነው? 
  • ገዥው ፓርቲ ከሠራቸው ሁሉ የሚበልጠው ትልቁ ነገር የአስተዳደር ወሰኑን ማካለሉ ነው መባሉ።
  • ለምን አስገረመህ? 
  • ትልቅ ነገር አይደለማ፡፡ 
  • እንዴት? ለምን?
  • ጥያቄውን ያነሳነው እኛው ነን፣ ለፖለቲካ ትግል ብለን ራሳችን ያነሳነውን ጥያቄ ሥልጣን ላይ ወጥተን መልስ መስጠታችን ተዓምር አይደለም ብዬ ነው። 
  • ጅል፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እየሰደቡኝ ነው?
  • ስድብ አይደለም።
  • ጅል አሉኝ እኮ?
  • ስድብ አይደለም ስልህ፡፡
  • ታዲያ ምን ማለት ነው?
  • እንደ ፓርቲ አባል ሳይሆን አንደ ማኅበረሰብ አንቂ ወይም አክቲቪስት ነው የጠየቅከው ለማለት ነው፣ እነሱ ናቸው የነቁ መስሏቸው እንዲህ ዓይነት ጥያቄ የሚያነሱት።
  • በእርግጥ ይህኑኑ ጥያቄ አንዳንድ ታዋቂ ሰዎች በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ሲያነሱ ተመልክቻለሁ ቢሆንም ተገቢ ጥያቄ ይመስለኛል።
  • ጅላ ጅል፡፡
  • ጅላ ጅል አሉኝ ክቡር ሚኒስትር? ጆሮዬ መሆን አለበት፡፡ 
  • ጆሮህ አይደለም፡፡ 
  • እና ምን አጠፍቼ ነው የሰደቡኝ ታዲያ? 
  • ስድብ አይደለም፡፡
  • ጅላ ጅል ስድብ ካልሆነ ምን ሊሆን ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ለራሳቸው ሳይነቁ ማኅበረሰብ አንቂ ነን የሚሉ ጅል ናቸው አላልኩህም? 
  • ባልስማማበትም ብለውኛል። 
  • አዲሱ ዕይታችን ነው፣ የአንተ መስማማት አስፈላጊ አይደለም። 
  • እሺ… ምን ይደረጋል… ይሁን፣ ስለዚህ ጅላ ጅል ማለት ምን ማለት ነው?
  • ጅሎችንና ሐሳባቸውን ለሚከተሉ የተሰጠ ስያሜ ነው። 
  • በአዲሱ የድርጅታችን ዕይታ ማለት ነው? 
  • አዎ፣ ልክ ነው፡፡ 
  • እኔ የምልዎት ክቡር ሚኒስትር?
  • እህ…
  • ሐሳቦችን ለመፈረጅ ጊዜ ከምናጠፋ ጥያቄዎችን ብንመልስ አይሻልም? 
  • አሁን ደግሞ ምን እንደምትባል ታውቃለህ?
  • ምን እባላለሁ?
  • ጅላንፎ! 

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአንድ አብሮ አደግ ወዳጃቸው ጋር በመኖሪያ ቤታቸው ሆነው ስለአገር ጉዳይ እየተጨዋወቱ የዕረፍት ቀናቸውን እያሳለፉ ነው] 

  • እኔ ምልህ ክቡር ሚኒስትር?
  • እንዲያው ይኼን ክቡር ሚኒስትር ማለት ተወኝ አላልኩህም?
  • አንተ ባትፈልግም ለተቋሙ ክብር መንፈግ ባህላችን አይደለም፣ ይልቅ ልጠይቅህ የነበረውን አስረሳኸኝ፡፡
  • ምን ልትጠይቅ ነበር?
  • አዎ፣ አስታወስኩት፣ እኔ የምልህ?
  • እህ…
  • መንግሥት በተደጋጋሚ ጊዜ ለሰላም ዝግጁ ነኝ እያለ በይፋ እየገለጸ ነው። አይደለም?
  • ትክክል ነው እሱማ፣ እነሱም ሰላም እንፈልጋለን ይላሉ፡፡ ታዲያ ሰላም ማውረድ ለምን አልተቻለም? ችግሩ ምንድነው?
  • ግራ ተጋብተው ግራ እያጋቡን መሆኑ ነው ችግሩ።
  • እንዴት? 
  • ሰላም እንፈልጋለን ይላሉ፣ ግን ደግሞ ግራ የሚያጋባ ቅደመ ሁኔታ ያስቀምጣሉ።
  • ምንድነው ግራ የሚያጋባው ቅድመ ሁኔታ? 
  • ለሰላም ዝግጁ ከሆናችሁ በቅድሚያ መግባት አለባችሁ ይሉናል፡፡ 
  • መግባት አለባችሁ ይሉናል ነው ያልከው ክቡር ሚኒስትር? 
  • አዎ።
  • ወዴት?
  • እነሱ ወደ የሚያስተዳድሩት ክልል። 
  • ለምን? ምን እንድታደርጉ ነው?
  • ቴሌ፣ ባንክና ሌሎች አገልግሎቶችን እንድንጀምር። 
  • አገልግሎት ለማግኘት ብለው ነዋ፡፡
  • አዎ፣ ግን ደግሞ ንግድ ባንክም ሆነ ቴሌ የፌዴራል መንግሥት ተቋማት ናቸው።
  • እሱማ ልክ ነው፣ በተጨማሪም የፌዴራል መንግሥት በየትኛውም አካባቢ የመሰማራት መብት አለው። 
  • አሱን ተወውና ያነሱትን ጥያቄ ተቀብለን ለመግባት ስንዘጋጅ ደግሞ ውጡ ይሉናል። 
  • ከየት? ገና ሳትገቡ?
  • ከምዕራቡ ወሰን ውጡ ይሉናል።
  • ሠራዊቱን ማለታቸው ነዋ፡፡
  • አንተ ራስህ የፌዴራል መንግሥት በየትኛውም አካባቢ መሰማራት ይችላል ስትል አልነበር እንዴ?
  • በእርግጥ ብያለሁ። 
  • ታዲያ የፌዴራል መንግሥቱን ሠራዊት ለምን ይውጣ ይላሉ?
  • ተመልከት አንዴ ሠራዊቱ ይውጣ ይሉናል፣ እዚያው ደግሞ አገልግሎት ሰጪ የፌዴራል ተቋማት ካልገቡ ይሉናል።
  • በመግለጫችሁ ላይ በኋላ ያላችሁት ነገር አሁን ነው የገባኝ፡፡
  • በኋላ ያልነው ምንድነው? 
  • መግባትና መውጣት! 

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የአየር መንገድ ተጓዦች በሻንጣ የሚያስገቡትን የልብስና የጫማ ብዛት የሚገድብ ረቂቅ መመርያ ተዘጋጀ

ከቀረጥ ነፃ ይገቡ የነበሩ ዕቃዎች 87 በመቶ እንዲቀንሱ ተደርጓል መንገደኞች...

ብሔራዊ ባንክ ለጥቃቅንና አነስተኛ ብድሮች ዋስትና መስጠት ሊጀምር ነው

ኢንተርፕራይዞችን ብቻ የሚያገለግል የፋይናንስ ማዕከል ሥራ ጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...

ነባር ‹‹ላዳ›› ታክሲዎችን መሸጥና መለወጥን ጨምሮ ለሌላ ማስተላለፍ ተከለከለ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተለምዶ ‹‹ላዳ ታክሲ›› ተብለው የሚታወቁትን...

አብን በደቡብ አፍሪካ የሚደረገው የሰላም ንግግር ይሳካል የሚል እምነት እንደሌለው ገለጸ

የፌዴራል መንግሥትና ሕወሓት ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ኩባንያ አስተዳደር ለኢትዮጵያ ባንኮች ውጤታማነት

የጠቅላላ ጉባኤ፣ የጥቆማና ምርጫ ኮሚቴ፣ የተቆጣጣሪ ቦርድ፣ የዳይሬክተሮች ቦርድና...

ጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አቶ ጌታቸው ረዳን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አድርገው ሾሙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ(ዶ/ር) አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል...

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...